የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የጅማ ዞን አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት ለገበያ በማቅረባቸው ተጠቃሚ ሆነዋል

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦ ቡናን በጥራት ለገበያ በማቅረባቸው ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን የጅማ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

አርሶ አደሮቹ ከልማዳዊ አሰራር በመላቀቅ ቡናን በባለሙያ ታግዘው በማልማትና በማዘጋጀት ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የጅማ ዞን ጮራ ቦቶር ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሁሴን ቶላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በግብርና ምርምር ማዕከልና በግብርና ጽሕፈት ቤት ባለሙያዎች ታግዘው የቡና ጥራትን ለማሻሻል ሲሰሩ ቆይተዋል።


በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጥና በሽታን የሚቋቋም የቡና ዝርያን ማልማታቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ቡናን ከምርት ጀምሮ ለገበያ እስከሚቀርብበት ጊዜ ድረስ ለጥራት ትኩረት መስጠታቸውን ተናግረዋል።

በዚህ ዓመት እስካሁን 5ሺህ ኪሎግራም ጥራቱን የጠበቀ ደረቅ ቡና አዘጋጅተው ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አሁን ላይ የገበያ ትስስር ችግር እንደሌለና በመንግስት በኩል ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት መሰጠቱ ተነሳሽነታቸው እያደገ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከአራት ዓመታት በፊት በግብርና ጽሕፈት ቤት ድጋፍ የተሻሻለ የቡና ዝርያ ቀርቦላቸው ማልማታቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ታጁ ያደታ ናቸው።


ቡናን ከአመራረት ጀምሮ በዝግጅትና ለገበያ እስከማቅረብ ሂደት ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የባለሙያ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ዘንድሮ የቡና ምርታቸውን በጥራት በመሰብሰብና በማዘጋጀት ለገበያ ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል።

በዘርፉም ከራሳቸው አልፈው ለሌሎችም የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አስታውቀዋል።

የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሚፍታህ ጋሊ፣ ዞኑ በቡና ምርት የሚታወቅ እንደመሆኑ ለምርቱ ጥራት ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ።


በተለይም ከጥቂት ዓመታት ወዲህ የገበያ ትስስርን በማስፋት፣ ለአምራቹ በቂ ግንዛቤና ስልጠና በመስጠት እንዲሁም ክትትል በማድረግ ትልቅ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።

በተጠናቀቀው በጀት አመት ጥራቱን ጠብቆ የተዘጋጀ 102 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው ለገበያ ከቀረበው ቡና ውስጥ 41 ሺህ ቶኑ የታጠበና ቀሪው ደረቅ መሆኑን ተናግረዋል።

የቡና ልማትን ለማስፋፋትና ጥራቱን የበለጠ ለማሳደግ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ የማድረስ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

ዘንድሮም 700 ሚሊዮን የቡና ችግኞችን በማሰራጨት ተከላው እየተካሄደ መሆኑን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026