የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከንጋት ሐይቅ ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት ተገኝቷል

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ከንጋት ሐይቅ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት መገኘቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ የተፈጠረው ግዙፍ ሰው ሰራሽ ሃይቅ (ንጋት ሃይቅ) የኤሌክትሪክ ሃይል ከማመንጨትና የቱሪስት መስህብ ከመሆን ባለፈ በዓሳ ምርት የስራ እድል መፍጠር ችሏል።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ላይ የተንጣለለው የንጋት ሃይቅ ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት ሲሆን በአካባቢው ልዩ ድባብ በመፍጠር ተመራጭ የመዝናኛ ስፍራ የሚሆን ነው።

የንጋት ሃይቅ በተለይም ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና አካባቢው ነዋሪዎች ተጨማሪ የኢኮኖሚ መሰረቶችን ይዞ የመጣ አቅም ሆኗል።

የንጋት ሐይቅ የዓሣ ሃብት ልማት፣ የቱሪዝምና የውስጥ ለውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲሁም በአካባቢው አዲስ የሥነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ሚዛን ለማስጠበቅ የሚያስችል ነው።


የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳት እና የዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢትቻ (ዶ/ር)፤ በንጋት ሐይቅ ዓሳ ማስገር ስራ 46 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከንጋት ሃይቅ ብቻ 1ዐ ሺህ 799 ቶን ዓሳ ማምረት መቻሉን ጠቅሰው በክልሉ የዓሳ ምርት እድገት ማሳያቱን ተናግረዋል።

የተገኘው ምርት ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ መጨመሩን ገልጸው በቀጣይም ተጨማሪ ማህበራት ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።


በክልሉ ከንጋት ሀይቅ በተጨማሪ ከዳቡስ፣ ዲደሳ እና በለስ ወንዞች የዓሳ ምርት በብዛትና በጥራት መመረቱን አንስተው በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ከክልሉ የዓሳ ምርት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም ከተሞች ለገበያ በማቅረብ ሁነኛ የገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ዶ/ር ብርሃኑ ገልጸዋል።


የንጋት ሐይቅ በተለይም በዓሳ ምርት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ዓሳ በማስገርና ለገበያ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ ከራሳቸው አልፈው ለቤተሰባቸው ጭምር መትረፋቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026