የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከንጋት ሐይቅ ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት ተገኝቷል

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፡- ከንጋት ሐይቅ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10 ሺህ 700 ቶን በላይ የዓሳ ምርት መገኘቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ የተፈጠረው ግዙፍ ሰው ሰራሽ ሃይቅ (ንጋት ሃይቅ) የኤሌክትሪክ ሃይል ከማመንጨትና የቱሪስት መስህብ ከመሆን ባለፈ በዓሳ ምርት የስራ እድል መፍጠር ችሏል።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ላይ የተንጣለለው የንጋት ሃይቅ ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት ሲሆን በአካባቢው ልዩ ድባብ በመፍጠር ተመራጭ የመዝናኛ ስፍራ የሚሆን ነው።

የንጋት ሃይቅ በተለይም ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና አካባቢው ነዋሪዎች ተጨማሪ የኢኮኖሚ መሰረቶችን ይዞ የመጣ አቅም ሆኗል።

የንጋት ሐይቅ የዓሣ ሃብት ልማት፣ የቱሪዝምና የውስጥ ለውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲሁም በአካባቢው አዲስ የሥነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ሚዛን ለማስጠበቅ የሚያስችል ነው።


የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳት እና የዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢትቻ (ዶ/ር)፤ በንጋት ሐይቅ ዓሳ ማስገር ስራ 46 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከንጋት ሃይቅ ብቻ 1ዐ ሺህ 799 ቶን ዓሳ ማምረት መቻሉን ጠቅሰው በክልሉ የዓሳ ምርት እድገት ማሳያቱን ተናግረዋል።

የተገኘው ምርት ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ መጨመሩን ገልጸው በቀጣይም ተጨማሪ ማህበራት ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።


በክልሉ ከንጋት ሀይቅ በተጨማሪ ከዳቡስ፣ ዲደሳ እና በለስ ወንዞች የዓሳ ምርት በብዛትና በጥራት መመረቱን አንስተው በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ከክልሉ የዓሳ ምርት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም ከተሞች ለገበያ በማቅረብ ሁነኛ የገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ዶ/ር ብርሃኑ ገልጸዋል።


የንጋት ሐይቅ በተለይም በዓሳ ምርት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ዓሳ በማስገርና ለገበያ በማቅረብ በሚያገኙት ገቢ ከራሳቸው አልፈው ለቤተሰባቸው ጭምር መትረፋቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026