የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ሞሪሺየስ እና ኢትዮጵያ ትብብራቸውን ማጠናከር የሚችሉባቸው ሰፊ እድሎች አሉ - የሞሪሺየስ ፕሬዝዳንት ድሃራምቢር ጎኩል

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ሞሪሺየስ እና ኢትዮጵያ ጤና እና ትምህርትን ጨምሮ የሁለትዮሽ ትስስራቸውን ማጎልበት የሚችሉባቸው አዳዲስ ዘርፎች መኖራቸውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ድሃራምቢር ጎኩል ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባና በፖርት ሉዊስ መካከል በሳምንት ሦስት ጊዜ የሚደረግ ቀጥታ የመንገደኞች በረራ በይፋ አስጀምሯል።

የሞሪሺየስ ፕሬዝዳንት ዳህራምቢር ጎኩል የአየር መንገዱን የቀጥታ በረራ መጀመር አስመልክቶ ለፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (Pulse of Africa Media POA) እንደገለጹት፤ ጠንካራ የአየር ትስስር የአፍሪካን የኢኮኖሚ አቅም ለማጎልበት ወሳኝ ነው።

አየር መንገዱ ወደ ሞሪሺየስ የጀመረው የቀጥታ በረራ በሀገራቱ መካከል በቱሪዝም፣ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በሰው ኃይል ልማት ዘርፎች አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥር አመልክተዋል።

ጠንካራ የአየር ትስስር የአፍሪካን ሙሉ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በረራው መጀመሩ የአፍሪካ ህብረት ይበልጥ የተቀናጀች አህጉር ለመፍጠር የሰነቀውን ራዕይ የሚያሳልጥ ነው ብለዋል።

ጠንካራ የአየር ትስስር የአፍሪካን ሙሉ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም ወሳኝ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

በአፍሪካ አህጉር ከሚገኙ ታላላቅ ተግዳሮቶች መካከል የትስስር አለመጠናከር ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ሞሪሺየስን ከኢትዮጵያ ጋር በማገናኘት፣ አፍሪካ ይህንን የቆየ እንቅፋት ለመቅረፍ ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ይህ አዲስ የበረራ መስመር ከመንገደኞች ማጓጓዝ ባለፈ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ለማጠናከር ትልቅ አቅም እንደሆነም አብራርተዋል።

ሞሪሺየስ ለዓለም አቀፍ ባለሀብቶችና የንግድ ተቋማት ዋነኛ የአፍሪካ መግቢያ በር ለመሆን እየሰራች መሆኑን ጠቁመውም፤ ይህንን ራዕይ ለማሳካት ጠንካራ የአየር ትስስር መፍጠር ቁልፍ ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለው ሰፊ የአፍሪካና የዓለም አቀፍ የበረራ ተደራሽነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድገውም ጠቁመዋል።

የጭነት ትራንስፖርት (ካርጎ) ከአፍሪካ ዋና ዋና የአቅርቦት ማነቆዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ አዲሱ አጋርነት በአህጉሪቱ ያለውን የዕቃዎች ዝውውር ለማሻሻል ትልቅ ተስፋ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

በጋራ መሥራታችን ይህንን የአቅርቦትና የዕቃዎች ዝውውር ችግር ለመፍታት ሰፊ ዕድል ይፈጥርልናል ሲሉም አክለዋል።

የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ለሞሪሺየስ ወጣቶች የአውሮፕላን አብራሪነትን ጨምሮ በሌሎች የአቪዬሽን የሙያ ዘርፎች የላቀ የአቅም ግንባታና የስልጠና ዕድሎችን እንደሚከፍት ጠቁመዋል።

በቀጣይም በትምህርት፣ በጤና እና በሰማያዊ ኢኮኖሚ (Blue Economy) ዘርፎች ዕውቀትን፣ ቴክኖሎጂንና ልምድን በመለዋወጥ በጋራ ለመሥራት ሰፊ ዕድል እንዳለ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ሞሪሺየስ በሳምንት ሶስት ቀናት ቀጥታ የመንገደኞች በረራ መጀመሩ ይታወቃል።

ይህም መንገደኞች ወደ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ እስያ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና አሜሪካ በቀላሉ እንዲጓዙ በማድረግ የአህጉሪቱን ትስስር እንደሚያጠናክር ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026