የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የገበያ አማራጮችን በማስፋትና ህገ ወጥነትን በመቆጣጠር ለገበያ መረጋጋት የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ ፤ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፡- የገበያ አማራጮችን በማስፋት፣ የምርት አቅርቦትን በማሳለጥና ህገ ወጥነትን በመቆጣጠር ለገበያ መረጋጋት የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የተጠናቀቀው በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የአዲሱን በጀት ዓመት እቅድ የትውውቅ መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ እያካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም መሐመድ (ዶ/ር)፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገበያ አቅርቦትና ዋጋን በማረጋጋት ረገድ ብዙ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም የገበያ አማራጮችን በማስፋት፣ የምርት አቅርቦትን በማሳለጥና ህገ ወጥነትን በመቆጣጠር ለገበያ መረጋጋት የሚደረገው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ንግድንና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮናስ መላኩ፤ በከተማው የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት የምርት አቅርቦትና ተደራሽነት ላይ በቅንጅት መሰራቱን አንስተው ቀጣይነት የሚኖረው መሆኑን አረጋግጠዋል።

በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የወረዳዎች በየደረጃው ያሉ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026