የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአፍሪካን ዕድገት ለማሳለጥ በታማኝ መረጃና ማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ ማሳለፍ ያስፈልጋል

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካን ፈጣን ዕድገት ለማሳለጥ በታማኝ መረጃና ማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ ማሳለፍ እንደሚያስፈልግ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ለሁለት ቀናት የሚቆየው 14ኛው የአፍሪካ የፖሊሲ ጥናት ጉባኤ "ፖሊሲን በፈጠራ፣ አካታችና ግልጽ ማስረጃ ማጠናከር" በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።


በአህጉራዊ ጉባኤው ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የልማት አጋሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ለውጥ፣ የአየር ንብረት ጫና፣ የሕዝብ ቁጥር ዕድገትና የኢኮኖሚ ተግዳሮትን ለመቋቋም ታማኝና ጥራት ባለው መረጃ ላይ የተመሠረቱ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ይጠይቃሉ።

ኢትዮጵያም በመረጃ የተደገፈ የፖሊሲ ውሳኔ አሰጣጥን ለማጠናከር ባለ ስምንት አምድ ብሔራዊ የስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም ይፋ በማድረግ ወደ ሥራ መግባቷን ገልጸዋል።

የብሔራዊ ስታትስቲክስ ሥርዓትን በዘመናዊ የዲጂታል አሠራር በማሸጋገር የግብርናና የኢኮኖሚ ተቋማት ቆጠራ፣ የሕዝብና ጤና ዳሰሳ እንዲሁም የቤተሰብ ደህንነት ዳሰሳዎች መካሄዳቸውን ተናግረዋል።

የጥናት ውጤቶችና መረጃዎችን ከመሰነድ ባሻገር ወደ የበጀት ውሳኔዎችና የመንግሥት ፕሮግራሞች ተግባራዊ እርምጃ ሊቀየሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም እንደ የሰው ሠራሽ ዕውቀትና የሳተላይት መረጃ ያሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሲጠቀሙ የግል መረጃ ጥበቃን የሥነ-ምግባር መርሆችንና የሕዝብን እምነት መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፈቃዱ ፀጋ በበኩላቸው፣ ምርምርና ጥናት ከፖሊሲ ሂደት ተነጥሎ በሪፖርት ብቻ መቅረት የሌለበት ወሳኝ ጉዳይ ነው ብለዋል።


ተመራማሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች በቅርበት በመሥራት የጥናት ውጤቶችን ወደ ተግባራዊ የፖሊሲ ውሳኔዎች እንዲለወጡም ግፊት ማድረግ እንደሚኖርባቸው ጠቁመዋል።

የአፍሪካን የኢኮኖሚ ሽግግር፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የትምህርትና የቴክኖሎጂ ተግዳሮቶች ለመፍታት ዕውቀት፣ ፈጠራና ትብብር ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአፍሪካ የተፅዕኖ ግምገማ ተመራማሪዎች ኔትወርክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር አሞስ ንጁጉና፤ ለአህጉሪቱ የልማት ውጤታማነት ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ መንግሥታትና የልማት አጋሮች በትብብር መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።


የጥናት ውጤቶች በጥናት መድረኮች ብቻ ሳይወሰኑ ወደ ውሳኔ ሰጪዎች በመድረስ ለሕዝብ ፖሊሲዎችና ለልማት ውሳኔዎች ቀጥተኛ ግብዓት ሊሆኑ እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026