የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኮሪደር ልማት ትሩፋቶች፤ የከተሞች ህዳሴ

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተጀመረው ሰፊ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የመንገድ ጥገና ወይም የማስዋብ ስራ ብቻ ሳይሆን፤ የከተሞች አወቃቀር፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እና የማህበራዊ ህይወት ገጽታ ሙሉ በሙሉ የለወጠ ሥር ነቀል ከተማን የማደስ ትልቅ ስራ ነው።

የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፣ በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማቱ በአዲስ አበባ ከተገኘው ስኬት በመነሳት ወደ 75 በሚጠጉ የሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞችና ታዳጊ ከተሞች ተስፋፍቷል። ይህም ሀገሪቱ ከተበታተነና ጥራት ከጎደለው የመሰረተ ልማት አሰራር ወጥታ ወደ ዘመናዊና የተቀናጀ የከተሜነት ምዕራፍ መሸጋገሯን ያመላክታል።

የኮሪደር ልማቱ ከዚህ ቀደም የነበሩ የከተሞች መዋቅራዊ ችግሮችን በጥቅሉ የፈታ ሲሆን፤ ዋና ዋናዎቹ የለውጥ መስኮች በሚከተሉት ነጥቦች ይጠቃለላሉ።


አካታች የመንገድና የትራፊክ ፍሰት

ቀደም ሲል መንገዶች ለባለሞተር ተሽከርካሪዎች ብቻ ያደሉ በመሆናቸው ለትራፊክ መጨናነቅና ለሚከሰቱ አደጋዎች ምክንያት ሆነው ቆይተዋል። የኮሪደር ልማቱ ሰፊ የእግረኛ፣ የብስክሌትና የስፖርት ማሳለጫ መንገዶችን፣ አየር ላይና ከመሬት በታች ድልድዮችን እንዲሁም ዘመናዊ የታክሲና አውቶቡስ ማቆሚያዎችን አካቶ ተገንብቷል።

የተቀናጀ የመሬት ውስጥ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ

ተደጋጋሚ የመንገድ ቁፋሮዎችንና ብክነትን ለማስቀረት የውሃ፣ የኤሌትሪክ ኃይል፣ የቴሌኮም እና የፍሳሽ መስመሮች በመሬት ሥር እንዲያልፉ ተደርጓል። ይህም ከተሞችን በአየር ከተንጠለጠሉ ገመዶች ነፃ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪም በክረምት ወቅት የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ እያስቻሉም ይገኛሉ።

የ24 ሰዓት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና አረንጓዴ ሥፍራዎች፦

በኮሪደር ልማቱ ባዶና ቆሻሻ መጣያ የነበሩ ስፍራዎች ወደ አረንጓዴ መናፈሻዎችና የሕዝብ መዝናኛዎች ተቀይረዋል። ዘመናዊ የመንገድና የህንጻ መብራቶች መገጠማቸው ደግሞ የደህንነት ስሜትን በመጨመር የሌሊት የንግድ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃ አድርጓል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኮሪደር ልማትን በተመለከተ ምን አሉ?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደደገለጹት፣ የኮሪደር ልማቱ የመንገድ ግንባታ ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን የከተሞች ደረጃ የሚያሻሽልና የዜጎችን ሥነ-ልቦና የሚያንጽ ስትራቴጂያዊ ፕሮጀክት ነው። ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ሀገር ነች፤ ስለዚህ ከተሞቻችንም ያንን ታላቅነታችንን የሚመጥን ፅዱ፣ አረንጓዴ እና ዘመናዊ ገጽታ ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የሀገር ግንባታ ቀጣይነት ያለው ሂደት መሆኑን በመግለጽ፣ ይህ ልማት ድህነትንና ቆሻሻን አለመቀበልን የሚያሳይ፣ ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፍ ኢትዮጵያን የመስራት ጉዞ አካል መሆኑንም ጠቁመዋል። በተጨማሪም በአዲስ አበባ የተገኘው ተሞክሮ ወደ አርባ ምንጭ፣ ባህር ዳር፣ አዳማ፣ ሀዋሳ እና ድሬዳዋ በመስፋፋቱ ፕሮጀክቱ በመላ ሀገሪቱ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

ምሁራን በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ያነሳሉ።

የከተማ ፕላንና ዲዛይን ባለሙያ ኢንጂነር አበበ ደሴ እንደሚሉት፤ የኮሪደር ልማቱ ለብዙ ዓመታት ሳይቀናጁ የዘለቁ እንደ የውሃ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል፣ የቴሌኮም እና የፍሳሽ መስመሮች የመሳሰሉ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በአንድ ላይ አቀናጅቶ በመሬት ሥር እንዲያልፉ ማድረጉ የከተሞችን እድሜ የሚያራዝምና አላስፈላጊ ተደጋጋሚ ቁፋሮዎችን ያስቀረ ትልቅ ሙያዊ እርምጃ ነው።

የከተማ ልማትና አስተዳደር ምሁር በላይ አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማቱ የከተሞችን የቦታ አጠቃቀም ቅልጥፍና ያሻሻለ መሆኑን ይገልጻሉ። ቀደም ሲል ለቆሻሻ መጣያነትና ለሕገ-ወጥ ሥራዎች ይውሉ የነበሩ ቦታዎች ወደ ሕዝብ መናፈሻነትና አረንጓዴ ሥፍራነት መቀየራቸው የከተሞችን የሥነ-ምህዳር ሚዛን ለመጠበቅ እንደሚረዳ ነው የተናገሩት።

የኢኮኖሚ ምሁሩ ቆስጠንጢኖስ በርኸ ተስፋ(ዶ/ር)፤ የኮሪደር ልማት በምሽት ጭምር ንግድ ማካሄድ የሚቻልበት አውድ የፈጠረ መሆኑን ይጠቅሳሉ። የከተሞች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በማሳለጥ በኩል ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ነው ያሉት።

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ፣ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የኢትዮጵያን ከተሞች ከነበሩበት የተጨናነቀና ኋላቀር ገጽታ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ፣ ፅዱ እና ለኢንቨስትመንት ሳቢ ወደሆኑ የከተማ ማዕከላት የመቀየር ትልቅ አዎንታዊ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ይህም የኢትዮጵያን ገጽታ በመቀየር በአፍሪካም ተጠቃሽ ሀገር እያደረጋት ይገኛል፤ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያም የኮሪደር ልማት ሰፊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ከመሆኑም ባለፈ ፕሮክቶችን በአጭር ጊዜ ጀምሮ የመጨረስ ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026