የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በብሄረሰብ አስተዳደሩ 34 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ፤ ሃምሌ 18/2018(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 34 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የአስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደገለፁት አካባቢው ዝናብ አጠር በመሆኑ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በስፋት በመገንባት ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከ539 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ 34 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸዋል።

የተገነቡት የመስኖ ፕሮጀክቶችም 820 ሄክታር መሬት በማልማት ከአራት ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።

ፕሮጀክቶቹ በብሄረሰብ አስተዳደሩ በበጋ ወቅት ጭምር በማምረት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

ስራ የጀመሩት ፕሮጀክቶች አርሶ አደሩ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ አትክልትና ፍራፍሬ ጨምሮ እንዲያመርትና የስርዓተ ምግብ ችግር እንዲያቃልል የሚያደርግ መሆናቸውንም ጨምረው ገልፀዋል።

የሰቆጣ ከተማ የ03 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ንጉሱ አመረ እንዳሉት፤ በአካባቢያቸው የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ከዝናብ ጥገኝነት በመውጣት በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ የማምረት አቅም እንድናገኝ የሚያደርግ ነው ።

የጓሮ አትክልትና ፍሬፍሬ እንዲሁም ሌሎች የሰብል ምርቶችን በማሳደግ አኗኗራቸውን ለመቀየር የሚያስችላቸው መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል።

በአስተዳደሩ በጋዝጊብላ ወረዳ 03 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አገኘሁ ጌታሁን፤በቀበሌያቸው የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት በክረምት ዝናብ ብቻ የተመሰረተውን የግብርና ስራ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚነታችን እንድናሳድግ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት በተገነቡ የመስኖ ተቋማት አራት ሺህ 885 ሄክታር መሬት ማልማት መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026