የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የመጠባበቂያ እህል ክምችትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቋቋም የሚያስችል የመጠባበቂያ እህል ክምችትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት አመራርና ድጋፍ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ገለጸ።

ከ300 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይም ለዚሁ ተግባር የሚውል የበቆሎ ልማት እየተከናወነ መሆኑ ተመላክቷል።


የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ኃይሉ ሀሰና እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚያጋጥሙ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመመከት የሚያስችል አቅም ለመገንባት እየተሰራ ነው።

በክልሉ አምስት ወረዳዎች ውስጥ የወል መሬትን በመጠቀም በቆሎ፣ ቦሎቄና ሌሎች ሰብሎችን በማምረት የመጠባበቂያ እህል ክምችት አቅምን የማሳደግ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም ከ300 ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ በቆሎ እየለማ እንደሚገኝ ጠቅሰው ከ12 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

ከዚህም ባለፈ ህብረተሰቡ በ"ካላሞ ፎጮ" ስርዓት እርስ በእርሱ የሚረዳዳበትን ባህል የማጎልበት ተግባር እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ይህም አርሶ አደሩ እህል በሚሰበሰብበት ጊዜ ከሚያገኘው ምርት ለወገኖቹ እንዲያጋራ በማድረግ የገንዘብ፣ የአልባሳትና የቁሳቁስ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም በዝናብ መስተጓጎል ምክንያት ማሳቸው የተጎዳባቸው አርሶ አደሮች የማካካሻ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ እንዲደርሳቸው መደረጉንም አክለዋል።


በክልሉ የደራራ ወረዳ አርሶ አደር በላይ ግዴሳ፤ በሁለት ሄክታር ማሳ ላይ ካለሙት የበቆሎ ምርት ላይ በባህላዊ የመረዳጃ ስርዓቱ "ካላሞ ፎጮ" መሰረት እስከ አምስት ኪሎ ግራም ረዳት ለሌላቸው ወገኖች እንደሚለግሱ ገልጸዋል።


የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አለማየሁ ዲጋ በበኩላቸው፤ ከሚያገኙት የበቆሎ ምርት ላይ እስከ አምስት ኪሎ ግራም ለተቸገሩ ወገኖች መርጃ እንዲሆን በ"ካላሞ ፎጮ" በኩል እንደሚለግሱም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት ተደርጓል

ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...

Jul 20, 2026

በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት እየጣለ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...

Jul 7, 2026

በተያዘው ዓመት በኢንዱስትሪው የተኪ ምርቶች አቅርቦትን በማሳደግ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተያዘው ዓመት የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግና የውጭ ምርቶችን በመተካት አምስት ቢሊዮን ዶላር ...

Jul 3, 2026

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026