🔇Unmute
ሃዋሳ፣ ነሀሴ1/2018(ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለኢንዱስትሪ ልማት መስፋፋት ምቹ መደላድል መፍጠሩን የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።
የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሃዋሳ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ እንደገለጹት በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለኢንዱስትሪ ልማት መስፋፋት ምቹ መደላድል ፈጥሯል።
ይህም የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በማሳደግ ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅምን እያሳደገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይም የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ይበልጥ ለማሳደግ መስረተ ልማቶችን በቅንጅት የማሟላት ሥራው በቀጣይም ይጠናከራል ብለዋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበሬ በበኩላቸው በክልሉ የኢንዱስትሪ አቅምን በማጠናከር የማምረት አቅምን የማሳደግ፣ የስራ ዕድል የመፍጠር፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን መጠን የመጨመርና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት ሥራ በትኩረት መከናወኑን ጠቁመዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ249 በላይ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ሥራ የማስገባትና ነባሮቹን በመደገፍ ከ22 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ ከክልሉ 14 ሺህ 500 ቶን የኢንዱስትሪ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ 155 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱንም አቶ አሻግሬ ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይ 290 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት ተችሏል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...
Jul 31, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026
ድሬደዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ ጥረት መደረጉን የድሬደዋ አስተዳ...
Jul 20, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በመረጃ የተደገፈ ውሳኔ አሰጣጥ በክልሎች መካከል የተመጣጠነ ልማት ከማረጋገጥ አንጻር ጠንካራ መሰረት መጣል መቻሉን የፌ...
Jul 7, 2026