የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ዓመታት ከ96 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል -አቶ አወሉ አብዲ

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል የሕዝቡን እርካታ የሚያረጋግጡና የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያዘምኑ ዘመናዊ ተቋማትን የመገንባትና የማደራጀት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ ተናገሩ።

በኢትዮጵያ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር፣ የቢሮክራሲና የዘመናዊ አሰራር እጥረት ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ሀገራዊ የሪፎርም ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

በዚህም መሠረት በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሕዝቡን እርካታ የሚያረጋግጡ፣ አሰራርን ግልጽና ቀልጣፋ የሚያደርጉ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን መሠረት ያደረጉ ተቋማዊ ማሻሻያዎች ተደርገዋል።

ይህ የአገልግሎት አሰጣጥን የማዘመንና ዘመናዊ ተቋማትን የመገንባት እንቅስቃሴም የቢሮክራሲ እንግልትንና ሙስናን በመቀነስ፤ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ፣ ዘመናዊ የአገልግሎት ማዕከላትን በመገንባትና የመንግሥት መዋቅርንና የሰው ኃይል አቅምን በማሳደግ ረገድ ውጤቶች እንዲመዘገቡ አስችለዋል።

በአጠቃላይ በክልሉ የሚከናወኑት እነዚህ የቴክኖሎጂና የተቋማት ግንባታ ሥራዎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመመለሳቸው ባሻገር፣ ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መፋጠን ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉ።

በዛሬው ዕለትም የዚሁ ጥረት አካል የሆነው እና ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የጅማ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ህንፃ ተመርቋል።


በምረቃው ላይ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝደንት አወሉ አብዲ፣ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ነመራ ቡሊ እና የተለያዩ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።


አቶ አወሉ አብዲ፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች ከ96ሺህ በላይ የልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቶቹም የህብረተሰቡን ጥያቄ ባማከለ መልኩ የተገነቡ መሆናቸውንም አክለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በክልሉ 96 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ተገንብተው የተቀላጠፈ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ ነው ያሉት።

"ወደፊትም ለህዝባችን የገባነውን ቃል በተግባር የመወጣት ሀላፊነታችንን ለማሳካት በትጋት እንሰራለን" ብለዋል።

በአጠቃላይ በክልሉ በመደመር እሳቤ የተተገበሩ ተግባራት በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚው ዘርፎች ትልቅ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ነመራ ቡሊ በበኩላቸው፤ ብልፅግና ፓርቲ በክልሉ ጠንካራ ኢኮኖሚን ለመገንባት እና ትምህርትና ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት እንዲሁም ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት ያደረጋቸው ጥረቶች ውጤታማ ናቸው ብለዋል።

ባለፉት ስድስት እና ሰባት ዓመታት በክልሉ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እድገት መመዝገቡንም ለአብነት አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ምርታማነትን በማሳደግ እና የስራ ዕድልን በማስፋት ረገድ ፓርቲው ለህዝብ የገባውን ቃል እየተወጣ መሆኑን አክለዋል።


ዛሬ የተመረቀው የአስተዳደር ህንፃ 125 ክፍሎች ያሉት እና 17 የመንግስት ሴክተሮች አገልግሎት የሚሰጡበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት ውጤታማነትን አሻሽሏል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...

Jul 31, 2026