የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የዲጅታል ሚዲያ አማራጮችን ለጋራ ትርክት ግንባታ ለማዋል ወጣቶች የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ ፤ነሐሴ 9/2018 (ኢዜአ )፡- የዲጅታል ሚዲያ አማራጮችን ለጋራ ትርክት ግንባታ፣ ለሀገር ልማትና በጎ ተግባራት ለማዋል በመትጋት ወጣቶች የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስገነዘበ።

ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና አመራሮች እንዲሁም ለወጣቶች በዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም፣ በጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን የመከላከል እንዲሁም በሐቅ ማጣራት ዙሪያ በዲላ ከተማ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ምስራቅ ጌቱ፤ በተለይም ወጣቶች የዲጂታል ሚዲያን ለልማትና ለሀገር ግንባታ በማዋል ለሁሉም የምትመች ሀገር በጋራ ለመገንባት አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለባቸው አንስተዋል።

በዲጂታል ሚዲያ የሚሰራጩ መረጃዎችን ትክክለኛት፣ እውነታና ሀቅ ማጣራት ተገቢ መሆኑን አንስተው፤ አፍራሽና ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የግል ጥቅማቸውን አስበው የሚሰሩ እንዳሉ አንስተዋል።


በመሆኑም የዲጅታል ሚዲያ አማራጮችን ለጋራ ትርክት ግንባታ ለሀገር ልማትና በጎ ተግባራት ለማዋል በመትጋት ወጣቶች የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚባ አስገንዝበዋል።

በየደረጃው የሚገኙ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያና አመራር አንዲሁም ተጽኖ ፈጣሪ ወጣቶች ለዘላቂ ሰላምና ልማት አሻራቸውን ለማኖር እንዲተጉ ጠይቀዋል።


የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ፤ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በብዛት ለጥላቻ ንግግር እና ለሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የተጋለጡ በመሆናቸው ሃቅን በማጣራት ለትክክለኛ መረጃ ስርጭት መትጋት ያስፈልጋል ብለዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያን ጅምር ስራዎች በማጠናከር ለሀገር ልማት መስራትና ለእውነት መትጋት በተለይም ከወጣቶች ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት ውጤታማነትን አሻሽሏል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...

Jul 31, 2026