የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አረንጓዴ አሻራ ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር መቀናጀቱ ውጤታማ አድርጎናል-አርሶ አደሮች

Aug 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውሃ፤ ነሐሴ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር በማቀናጀት ተጠቃሚ መሆናቸውን የዞኑ አርሶ አደሮች ገለጹ።


በዞኑ የቆላ ፍራፍሬ ልማትን በኩታ ገጠም እርሻ ለማልማት ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ ይገኛል።


በልማቱ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አርሶ አደር ደሴ ባይተኩስ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ጋር አስተሳስረው በመስራታቸው አመርቂ ውጤት አግኝተዋል።


በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ያለሙትን ሙዝና ማንጎ ለገበያ በማቅረብ ከ150 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ነው የሚናገሩት።


በተለይ "በክላስተር መደራጀታችን የውሃ አጠቃቀማችንን እና የግብዓት አቅርቦት ችግራችንን አቃልሎልናል" ያሉት አርሶ አደሩ፣ በዘንድሮው ዓመትም የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


ሌላኛዋ የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ፀጋነሽ ብዙነህ በበኩላቸው፥ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በስፋት ለመሳተፍና ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችል ዕድል ይዞ መምጣቱን ገልጸዋል።


ሁለት ሄክታር በሚጠጋ መሬት ካለሙት ሙዝ፣ ማንጎና


ፓፓያ ከእለት ፍጆታ በተጨማሪ ለገበያ የሚተርፍ ምርት በማምረት ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፥ በዞኑ በ1 ሺህ 113 ሄክታር መሬት ላይ የቡናና የቆላ ፍራፍሬ ልማት እየተካሄደ ይገኛል።


ከዚህ ውስጥ 200 ሄክታሩን በክላስተር በፓፓያና በሙዝ ለማልማት በተጀመረው ስራ እስካሁን ከ40 ሄክታር በላይ መሬት መሸፈኑን ገልጸዋል።


የፓፓያና የሙዝ ክላስተር ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋት መምሪያው ልዩ ትኩረት መስጠቱን የጠቀሱት ኃላፊው፥ አስፈላጊው ግብዓት በወቅቱ ለአርሶ አደሮች እንዲሰራጭ መደረጉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት ውጤታማነትን አሻሽሏል

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓትንና የወጪ ውጤታማነትን ማ...

Jul 31, 2026