የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቁልፍ መሰረተ ልማት የሳይበር ደኅንነት አዋጅን ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚያስችል የውይይት መድረክ ተካሄደ

Aug 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማት የሳይበር ደኅንነት አዋጅን ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚያስችል የውይይት መድረክ መካሄዱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር (ኢመደአ) አስታወቀ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከቁልፍ መሰረተ ልማት አስተዳዳሪ ተቋማት ከተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በቁልፍ መሰረተ ልማቶች የሳይበር ደኅንነት አዋጅ (ቁጥር 1426/2018) እና በሴክተር መለያ ስታንዳርድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል።


የኢመደአ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ጉታ በወቅቱ አዋጁን ወደ ተጨባጭ ትግበራ ለማሸጋገር የመጀመሪያውና መሠረታዊው ተግባር በወጣው ስታንዳርድ መሠረት ቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማትን መለየትና መመደብ መሆኑን ገልጸዋል።

የሀገራችንን ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ከሳይበር ስጋቶችና ጥቃቶች መጠበቅ የኢትዮጵያን አጠቃላይ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ደኅንነት ከማረጋገጥ፣ ብሔራዊ ሉዓላዊነትን ከመጠበቅና ሀገራዊ ጽናትን ከመገንባት አንፃር ወሳኝ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።

በመድረኩ ላይ የአዋጁን አጠቃላይ ይዘት የሚያስተዋውቅ ገለጻ የቀረበ ሲሆን፣ አዋጁ ሀገራዊ የሳይበር ደኅንነትን ለማጠናከር፣ የጉዳት ስጋቶችን ለመቀነስ እና ለተቋማት ጥበቃ ግልጽ የሕግ ማዕቀፍ የሚዘረጋ መሆኑ ተብራርቷል።

በተጨማሪም "Critical Infrastructure and Sector Designation Standard" በሚል ርዕስ በቀረበው ገለጻ፣ ተቋማት በምን መስፈርት፣ ሂደትና የስጋት ግምገማ (Risk-based methodology) ቁልፍ ተብለው እንደሚለዩና ደረጃቸው እንደሚወሰን ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።


ስታንዳርዱ ተቋማት በሚሰጡት አገልግሎት ወሳኝነት፣ በስጋት ደረጃቸውና የሳይበር ጥቃት ቢደርስባቸው በሚያስከትሉት ሀገራዊ ተፅዕኖ ላይ ተመስርቶ ግልጽ አሰራርን የሚዘረጋ መሆኑ ተመልክቷል።

በውይይቱ ወቅት አዋጁንና ስታንዳርዱን በውጤታማነት ወደ መሬት ለማውረድ በኢመደአ እና በቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማት መካከል ሊኖር ስለሚገባው ቅንጅታዊ አሰራር፣ የጋራ ኃላፊነትና የትብብር ማዕቀፍ ላይ ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም አዋጁ ሀገራዊ የሳይበር ጥበቃን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ገልጸው፣ ለትግበራው በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን የተቋሙ መረጃ አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026