የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ውጤታማ የልማት ስራዎች ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ተሞክሮ ናቸው

Aug 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ውጤታማ የልማትና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራት ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ተሞክሮ መሆናቸውን ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ ጎብኚዎች ገለጹ።

ከቦትስዋና የመጡትና በአዲስ አበባ ለቀናት ጉብኝት ያደረጉት ቲሞቲ ካጎ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፣ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ መጎብኘታቸውን ጠቁመው፤ በከተማዋ በተመለከቱት የልማት ተግባራት መደመማቸውን ገልጸዋል።

በቆይታቸው የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችን መጎብኘታቸውን፣ የልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራቱ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የወንዞቹን የቀድሞ ገጽታ መመልከታቸውን ጠቁመው፣ መሰል የተፈጥሮ ጸጋዎችን ወደ ልዩ የመዝናኛ ስፍራዎች መቀየር እንደሚቻል በአዲስ አበባ የተመዘገበው ውጤት ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።

በወንዝ ዳርቻዎች የተከናወኑ የልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራት ለመናፈሻነትና ለመዝናኛነት ከመዋላቸው ባለፈ፣ ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች መጎልበት የተገነቡ ሱቆችና አዳዲስ ሥራ ፈጠራዎች ማካተቱ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም ቁርጠኛ አመራር ካለ ትልልቅ የልማት ተግባራትን በማከናወን ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ያሳያል ነው ያሉት።

ይህ የልማት ሥራ የተፈጥሮ ጸጋዎችን እንዴት ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት መቀየር እንደሚቻል ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራት በትብብር ሲከናወኑ ምን ያህል ውጤታማ እንደሚሆኑ መታዘባቸውንም ገልጸዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን መጎብኘቷን የተናገረችው ካሜሮናዊቷ ወጣት ስዋዚ ኢቤል-ኤቤል፤ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቷ በፊት ስለ ኢትዮጵያ የልማት ተግባራትና ውጤታማነት ግንዛቤ ማግኘቷን አንስታለች።

በአዲስ አበባ ጉብኝቷ ኢትዮጵያ በአስደማሚ የልማት እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ መመልከቷንና ይህም ለአፍሪካ ተምሳሌት መሆኑን ጠቅሳ፣ የሕዝቡ እንግዳ ተቀባይነትም ልዩ እና የሚደነቅ ነው ብላለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026