የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል የቴክኖሎጂውን ዘርፍ ቁልፍ የእድገት መሳሪያ ለማድረግ እየተሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

Sep 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር ፤ ነሃሴ 28/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል የቴክኖሎጂውን ዘርፍ ቁልፍ የእድገትና የመወዳደሪያ መሳሪያ አድርጎ ለመጠቀም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።

በክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ "የኤሌክትሮኒክስ መንግስት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሰረት ነው" በሚል መሪ ቃል የፓናል የውይይት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳደሩ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት፣ በክልሉ ፈጠራና ቴክኖሎጂን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳለጫ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

በአማራ ክልል "ዲጂታል አማራ" በሚል በ25 ዓመቱ የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ ላይ ቴክኖሎጂ እንደ ልማት መዳረሻ መፍጠሪያ ተደርጎ ተይዟል ብለዋል።

በ25 ዓመቱ ስትራቴጂክ ግብ ላይ በ2042 የአማራ ክልል ዋነኛ ሀብት፤ የአገልግሎት መስጫ እና የኢኮኖሚ የዕድገት ምንጭ ቴክኖሎጂ እንዲሆን ይሠራል ነው ያሉት።

በዚህም ዘርፉን የሚመራውን ተቋም በአዲስ በማደራጀት፣ አሰራሮችን በመዘርጋትና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን አስረድተዋል።

በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ በቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን የታገዘ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት ለመስጠት ያስቻለ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።

በቀጣይም ተቋማት ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ የማምረትና አገልግሎት የመስጠት ተግባር ላይ አተኩረው እንዲሰሩ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግም አስገንዝበዋል።

የኢፌዴሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶር) በበኩላቸው፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ላይ በትኩረት በመስራት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025ን ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

ባለፈው አፈጻጻም የተገኘውን ተሞክሮ በመቀመርም አሁን ላይ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማትን በማሟላት የዲጂታል ግብይት፣ ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ የመንግስት አገልግሎትና ጉልበት የቀነሰ አመራረት እውን በማድረግ ለውጥ መመዝገቡንም አስረድተዋል።

ይህም የሰው ኃይሉን በኢትዮ ኮደርስ በማሰልጠን ጭምር በተሰማራበት የስራ ዘርፍ ሁሉ ውጤታማና በዓለም አቀፍ ጭምር ተወዳዳሪ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በአገራችን የሚገኘው ወጣት ኃይል ራሱን በቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት በማነጽ እየመጣ ያለውን ዓለም አቀፍ ውድድር ለማሸነፍ መዘጋጀት እንዳለበት አሳስበዋል።

በፓናል ውይይቱ ላይ የፌዴራልና የክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን በእለቱም የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ያዘጋጀው የቴክኖሎጂ ውጤቶች አውደ ርዕይ ለእይታ ክፍት ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026