የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሲዳማ ክልል በግብርናው ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ ተመዝግቧል

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፣ ‎ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል በግብርናው ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ መመዝገቡን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለጸ።

የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ያለፉት አምስት ዓመታት የዘርፉ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የሴክተር ጉባኤ ተካሂዷል።


በጉባኤው ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አስፋው ጎኔሶ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ዓመታት የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂና አሰራሮች በመጠቀም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በተለይ ህዝብን በማነቃነቅ የማይታረሱ መሬቶች ጭምር እንዲታረሱ ማድረግና አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በመስኖ በተከናወኑ ተግባራት አመርቂ ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በመስኖ የሚለማ መሬት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ገልጸው፣ አርሶ አደሩ በዓመት ከሦስት ጊዜ በላይ በማምረት ከራሱ ባለፈ ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው እንዳሉት በዘርፉ የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ ተቀርፆ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡

በዚህም የምግብና ሥርዓተ ምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ፣ ገበያ ተኮር እና ለኢንዱስትሪዎች ግብዐት የሚሆኑ ምርቶችን በስፋት የማምረትና በእሴት ሰንለት ውስጥ ሰፊ የሥራ ዕድል የመፍጠር ግቦች ተነድፈው በርካታ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

እነዚህን ግቦች ከማሳካት አንፃርም የተከናወኑ ተግባራት እመርታዊ ለውጥ እያሳዩ መምጣታቸውን አስረድተዋል።

ባለፉት አምስት ዓመታት በቆሎ፣ ገብስ፣ ስንዴና ጤፍን ጨምሮ በሲዳማ ክልል በዋና ዋና ሰብሎች ብቻ የማሳ ሽፋን ከነበረበት 70 ሺህ ሄክታር ወደ 123 ሺህ ሄክታር ማሳደግ እንደተቻለም ተናግረዋል።

በቡና ልማትም የተመረጡ ዝርያዎችን በማስፋትና መሰል ሥራዎችን በማከናወን ከአምስት ዓመት በፊት ከነበረበት 149 ሺህ ሄክታር ሽፋን አሁን ላይ 186 ሺህ ሄክታር ማድረስ መቻሉን አስረድተዋል፡፡

በሞዴል አርሶ አደሮች ደረጃ ያለውን የቡና ምርታማነት እድገት ወደ ሁሉም አርሶ አደሮች ለማስፋት በቀጣይ በትኩረት ይሰራል ሲሉም ገልጸዋል።

በጉባኤው ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026