የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የኳታር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሳተፉ ጥሪ አቀረቡ

Sep 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡- የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የኳታር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሳተፉና የሁለቱ አገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲጠናከር ጥሪ አቀረቡ።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ዱባይ እየተካሄደ ካለው ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባኤ (AIM Congress) ጎን ለጎን የኳታር ቻምበር የቦርድ አባል አሊ ቢን አብዱላቲፍ አል ሚስናድ ጋር ዛሬ መወያየታቸውን የኢዜአ ሪፖርተር ከሥፍራው ዘግቧል።


ውይይቱ የኳታር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለይም በግብርና፣ በጤና፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በማማከር አገልግሎትና በሌሎች የኢንቨስትመንት አማራጮች ተሳትፏቸውን ማሳደግ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል።

ፕሬዚዳንት ታዬ በወቅቱ፣ ኢትዮጵያ የውጭ ባለሀብቶችን ለመሳብና ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር መንግሥት ትኩረት አድርጎ የሚሠራቸውን ሥራዎች አብራርተዋል።

በዚህም የኳታር ባለሀብቶች በአገሪቱ ያሉትን ምቹና አስቻይ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲጠቀሙና ግንኙነታቸው ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አድርገዋል።


የኳታር ቻምበር የቦርድ አባል አሊ ቢን አብዱላቲፍ አል ሚስናድም በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የኳታር ባለሀብቶች በግብርና፣ በጤና፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ በተለይም በቤቶች ግንባታና በዲጂታል ልማት ዘርፍ ለመሳተፍ ፍላጎት አላቸው።

በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢ የኳታር ባለሀብቶች እንዲጠቀሙበት ለማድረግና በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026