🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ):-ሸገር ከተማ የህዝብ አገልግሎቷን ለማዘመንና የነገ ከተማ ራዕይን ለማሳካት ዲጂታል ሽግግሯን እያፋጠነች መሆኑን ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ጳጉሜን 5 የነገ ቀንን ምክንያት በማድረግ በኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የተገነባውን የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ህንፃን አስመርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
ከንቲባው በዚሁ ወቅት እንዳሉት ፤ ሸገር ከተማ የነገ ከተማ ራዕይን ለማሳካት ቴክኖሎጂን፣ ዲጂታላይዜሽንንና ዘላቂ የከተማ ልማትን በትኩረት እየተገበረች ነው።

ቴክኖሎጂ የሥራ ቅልጥፍናን ከማሳደግ ባለፈ ከህዝብ ጋር ያለውን ግንኙነትና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ወሳኝ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
ከተማዋ ከተመሠረተች ጀምሮ የመሬት፣ የኢንቨስትመንትና የተለያዩ ዘርፎች መረጃዎችን ዲጂታል በማድረግ ላይ መሆኗን ከንቲባው ገልጸዋል።
በተጨማሪም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በከተማዋና በአራት ክፍለ ከተሞች እየተሰጠ ሲሆን፣ ከ280 ሺህ በላይ ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የተመረቀው የመሶብ ዲጂታል አገልግሎት ህንፃ የከተማዋን ዲጂታል ሽግግር በማጠናከር የህዝብ አገልግሎቷን ይበልጥ ለማዘመን ያግዛል።
ስለ ቴክኖሎጂ፣ ስለ ዲጂታላይዜሽንና ስለ ነገ ቀን ሳናስብ ምንም ዓይነት ውጤት መፍጠር አንችልም ሲሉም ከንቲባው አስገንዝበዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026