የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>በክልሉ ከበልግ ወቅት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል- የግብርና ቢሮ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ ጥር 30/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በምግብ ራስን ለመቻልና ከተረጅነት ለመውጣት የስንዴ መስኖ ልማት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና ሌሎችም የግብርና ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑ ይታወቃል።

በክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማት ባለሙያ ኤልያስ በላይ ለኢዜአ እንዳሉት የበልግ እርሻ እየተከናወነ ያለው በክልሉ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት በተለይም በሰሜን ሸዋ፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በደቡብና ሰሜን ወሎ ዞኖች እንዲሁም ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በተያዘው የበልግ ወቅት 239 ሺህ 500 ሄክታር መሬት በማረስ ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ከ168 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መታረሱን አረጋግጠዋል።

ለበልግ እርሻ በተለያዩ ሰብሎች ከሚለማው መሬት 23 ሺህ 337 ሄክታሩን በስንዴ ሰብል ለመሸፈን የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለበልጉ የምርት እንቅስቃሴ ማዳበሪያና የምርጥ ዘርን ጨምሮ አጠቃላይ የግብርና ግብአት የማሟላት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በግብርና ልማት እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት የመውጣትና በምግብ ራስን የመቻል ጥረት መሆኑንና ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

በዚህም በዘንደሮው በልግ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው፤ አርሶ አደሮችም ጥሩ ዝግጅት እያደረጉ ነው ብለዋል።

በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በበልግ ወቅት ከለማው 228 ሺህ 455 ሄክታር መሬት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የቢሮው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026