የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>አዲስ አበባ በአሕመድ ሴኩ ቱሬ አንደበት</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

(62 ዓመታት ወደኋላ)

________________

አሕመድ ሴኩ ቱሬ ከቀደምት የፓን አፍሪካዊነት አቀንቃኞች አንዱ ነበር። በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር በነበረቸው የምዕራብ አፍሪካዊነቷ ሀገረ-ጊኒ የነጻነት ታጋይና ፖለቲከኛ ናቸው። ድሕረ ነጻነት የሀገሪቷ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ሆነዋል። በፈረንጆቹ አቀጣጥርግንቦት 1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ላይ ከታደሙና አስደማሚ ንግግር ካሰሙ መሪዎች መካከል አንዱ ሴኩ ቱሬ ነበሩ። ለዛሬ ከፕሬዝዳንት አሕመድ ሴኩ ቱሬ አዲስ አበባን እና ኢትዮጵያን በወቅቱ የገለጹበትን መንገድ እነሆ ብለናል።

“…. አዲስ አበባ የታሪክ ክስተት መውጠኛ ስፍራ ናት። በአፍሪካ አወንታዊ የለውጥ ሽግግር ታሪክ መቁጠሪያ ነጥብ ሆናለች። ይህ ቅጽበት የአፍሪካ የተሟላ አርነት ማብሰሪያ ነው፤ የአፍሪካ ሰው ከነምጣኔ ሀብታዊ፣ ማህበራዊ፣ ወታደራዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ውቅሩ ነጻ የሚወጣበት። ይህ ስፍራ አፍሪካዊያን መንግስታትን ውጤታማ የሚያደርግ የፈጠራ ክዋኔዎች የመለኮሻ ዘመንም ነው። ለምን ቢሉ አፍሪካዊያን ወደ አንድ በመመጣት ህዝባቸውን ከሰቆቃ እንዲያገግም፣ የጋራ ስልጣኔ እንዲያንሰራራ፣ ሰብዓዊ እሴቶችና ባህላቸው ፈጣን እመርታ እንዲያመጣ ግብ የሰነቁበት ነውና።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ትልቅ ነው። ኢትዮጵያዊያን ለአፍሪካ ነጻ መውጣት በጀግንነት ተዋግተዋል። የሕዝብ ነጻነት እንዲጠበቅ ብሎም ሰዎች ያለማንም የውጭ አካል ጣልቃገብነት መብታቸው ተከብሮ መዳረሻቸውን በራሳቸው ይተልሙ ዘንድ መንገድ የጠረጉ እና የራሳቸውን ጉዳይ በተሟላ ሉዓላዊነት እንዲፈጽሙ በተግባር ያሳዩ ህዝቦች ናቸው።

ዛሬ በኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ የአፍሪካ ጉባዔ እየተካሄደ ነው። ይህም ኢትዮጵያ ምንጊዜም በአፍሪካ ታሪክ ገጾች ውስጥ ደማቅ አሻራ አንብራለች። መላው የአህጉሪቷ ህዝብ የመለወጥ መሻቱን በቅጡ እንዲገነዘብ የተካሄደ ሁነት ነው።

በ1885ቱ(በአውሮፓዊያን አቆጣጠር) የበርሊን ጉባዔ በኢኮኖሚ የጠገቡ ስርዓት አልበኛ የአውሮፓ መንግስታት ስልጣኔያቸውን ለማስፋፋት ሲሉ ያላቸውን ሀይል ተመክተው አፍሪካን እንደ ኬክ ቆራርሰው ሊቀራመቱ ተሰባስበው ነበር። ዛሬ ግንቦት 1963(በአውሮፓዊያን) ግን ምርጥና ሐቀኛ የአፍሪካ ልጆች ስለራሳቸው እና ስለእናት ምድር አፍሪካ ታምነው በንጹህ ማንነት የጋራ መዳረሻ መንገድ ለመቀየስ አዲስ አበባ ተሰባስበው እየመከሩ ነው።

የአፍሪካ ትንሳኤዋ ዛሬ ነው። አፍሪካ በአንድ ነጠላ መንግስት ህጋዊ መልክ ትይዝ ዘንድ ልዩ መተዳደሪያ ሰነድ(ቻርተር) ማለትም አፍሪካዊያንን በወንድማማችነት፣ በማይናወጥ አጋርነት፣ በሰዎች መብትና ጥቅም፣ በሰላምና ነጻነት እንዲሁም በፍትህ መርሆች ውህደት የሚፈጥሩበት አጋጣሚ ነው።

የአዲስ አበባ ጉባዔ የዛሬን አፍሪካ ችግሮች ምላሽ በመስጠት ላይ ብቻ የተወሰነም አይሆንም። አፍሪካ የዓለም አካል መሆኗን ልብ ይሏል። በዓለም ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሰው ልጅ ሕይወት፣ ሰላም፣ ደህንንትና ዕድገት መንስኤ የሆኑ የጋራ ተግዳሮቶች ሁሉ አፍሪካን ይገዷታል…”።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026