የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የመንገድ ደህንነት ፈንድ የቦርድ አባል ሆነው ተሾሙ

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 03/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የመንገድ ደህንነት ፈንድ የቦርድ አባል ሆነው ተሾመዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሀገራዊ የመንገድ ደህንነት ስትራቴጂ በመቅረፅና የመንገድ ደህንነት ትምህርት በስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት በማድረግ የወሰደችው እርምጃ የመንገድ ደህንነትን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑ ለሚኒስትሩ በተጻፈ ደብዳቤ ተገልጿል፡፡

በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ስራዎች የተገነቡ ምቹ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዶች እንዲሁም የተሻሻሉ የመንገድ ትስስር ስራዎች እንደ ሀገር የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ቅንጅትን የሚያሳድጉ እንደሆኑ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ኢትዮጵያ በመንገድ ደህንነት ላይ ያላትን ቁርጠኝነትና የምታደርገውን ጥረት በመገንዘብና እውቅና በመስጠት ሚኒስትሩ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የመንገድ ደህንነት ፈንድ ስር የባለአደራዎች ቦርድ አባል ሆነው መሾማቸውን አሳውቋል፡፡

ይህም ኢትዮጵያ ልምዷን ለሌሎች ሀገራት እንድታጋራና ከመላው ዓለም በመንገድ ደህንነት ላይ የተሻሉ ተሞክሮዎችን እንድታገኝ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የመንገድ ደህንነት ፈንድ እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2018 የተመሠረተ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ ላላቸው ፕሮጀክቶች ተጨማሪ ገንዘብ የማሰባሰብ እና የመደገፍ ስራን የሚሰራ ዓለማቀፍ ድርጅት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.