
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የብራዚል የቢዝነስና ኢንቨስትመንት ፎረም ዛሬ በብራዚል ሳኦፖሎ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
በፎረሙ መክፈቻ ላይ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ፣ የብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር አንቶኒዮ ሴዛር፣ የኢትዮጵያና ብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች እና የሁለቱ ሀገራት የንግድ ማህበረሰብ አባላት ተገኝተዋል።
ፎረሙ የኢትዮጵያን እምቅ የኢንቨስትመንት፣ የንግድ እና ቱሪዝም አቅም ማስተዋወቅ ያለመ መሆኑን በብራዚል የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ያሏት ምቹ እድሎች አስመልክቶ የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ሁነቱ የኢትዮጵያ እና ብራዚልን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር የማጠናከር ፋይዳ እንዳለውም ገልጿል።
በፎረሙ ላይ በኢትዮጵያ እና ብራዚል የንግድ ተወካዮች መካከል የአንድ ለአንድ የቢዝነስ ውይይቶች እንደሚደረጉ ኤምባሲው አመልክቷል።
የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አቅም የሚያስተዋውቅ ፎረም በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ በተገኙበት በብራዚሊያ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026