የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ቤላሩስ ለኢትዮጵያ በባለብዝሃ ወገን መድረኮች ላይ የምትሰጠውን ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥል ጥሪ ቀረበ

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- ቤላሩስ ለኢትዮጵያ በባለብዝሃ ወገን መድረኮች ላይ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክር እንድትቀጥል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ራይዜንኮቭ ከተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

ውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀብት ልማትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለኢትዮጵያ ለሰጠችው ድጋፍ እና ላሳየችው የገለልተኝነት አቋም ምስጋናቸውን አቅርበው ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና በሌሎችም ዘርፎች በስፋት እየሰራችና አበረታች ውጤት እያስመዘገበች ይገኛል ብለዋል።

በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ከአጋር ሀገራት ጋር የምታደርገውን የትብብር ስራዎች ይበልጥ ትኩረት እንደምትሰጥ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ተወዳዳሪነትን በማጠናከር የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ለመፍጠር በመሰረተ ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ባለቤትነት ላይ ስኬታማነትን እንድታረጋግጥ የአጋር ሀገራት ትብብር ወሳኝ ሚና እንዳለውም ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት።

የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ራይዜንኮቭ በበኩላቸው ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራትና ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።

በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማዕድን፣ በንግድ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ላይ ከኢትዮጵያ የሚቀርቡ የአጋርነት ፍላጎቶችን በመንተራስ በትብብር ለመስራት ዝግጁ ናት ብለዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ቤላሩስን እንዲጎበኙም ጋብዘዋል።

የሁለትዮሽ ምክክሩ የሀገራቱን ትብብር ለማጠናከርና በተመረጡ ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ቀጣይነት ያለው ውይይት ለማድረግ ስምምነት ላይ መደረሱን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026