የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ቤላሩስ ለኢትዮጵያ በባለብዝሃ ወገን መድረኮች ላይ የምትሰጠውን ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥል ጥሪ ቀረበ

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ):- ቤላሩስ ለኢትዮጵያ በባለብዝሃ ወገን መድረኮች ላይ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክር እንድትቀጥል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ራይዜንኮቭ ከተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

ውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀብት ልማትና ሌሎች ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለኢትዮጵያ ለሰጠችው ድጋፍ እና ላሳየችው የገለልተኝነት አቋም ምስጋናቸውን አቅርበው ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና በሌሎችም ዘርፎች በስፋት እየሰራችና አበረታች ውጤት እያስመዘገበች ይገኛል ብለዋል።

በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ ከአጋር ሀገራት ጋር የምታደርገውን የትብብር ስራዎች ይበልጥ ትኩረት እንደምትሰጥ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ተወዳዳሪነትን በማጠናከር የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ለመፍጠር በመሰረተ ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ባለቤትነት ላይ ስኬታማነትን እንድታረጋግጥ የአጋር ሀገራት ትብብር ወሳኝ ሚና እንዳለውም ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት።

የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ራይዜንኮቭ በበኩላቸው ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራትና ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።

በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማዕድን፣ በንግድ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ላይ ከኢትዮጵያ የሚቀርቡ የአጋርነት ፍላጎቶችን በመንተራስ በትብብር ለመስራት ዝግጁ ናት ብለዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ቤላሩስን እንዲጎበኙም ጋብዘዋል።

የሁለትዮሽ ምክክሩ የሀገራቱን ትብብር ለማጠናከርና በተመረጡ ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ቀጣይነት ያለው ውይይት ለማድረግ ስምምነት ላይ መደረሱን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026