የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አበርክቶው የጎላ ነው - አቶ ጌቱ ወዬሳ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8 /2017(ኢዜአ)፦የፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አበርክቶው የጎላ መሆኑን የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ከሐረሪ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ጋር በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ መክሯል።

የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት በብልፀግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት ፋይዳ ዜጎች ወጥ ማንነት እንዲኖራቸው በማስቻል የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።


ከዜጎች የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ሙስናን በመከላከል የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑንም ገልፀዋል።

በተለይ የማጭበርበር ወንጀሎችን በማስቀረት የፋይናንስ ዘርፍ ደህንነትን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል።

የፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተያዙ ግቦችን በማሳካት አበርክቶው የጎላ መሆኑንም ነው የገለፁት።

በቀጣይም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አገልግሎት ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር እንደሚሰራ አክለዋል።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ምክትል ሀላፊ አቶ ኦላና አበበ በበኩላቸው ፋይዳ መታወቂያ የአገሪቱን ህዝብ ትክክለኛ መረጃ ለይቶ ለማወቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚያግዝ እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ዜጎች አገልግሎት የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚያመቻች ስለመሆኑ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026