
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8 /2017(ኢዜአ)፦የፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አበርክቶው የጎላ መሆኑን የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ከሐረሪ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ጋር በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ መክሯል።
የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት በብልፀግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት ፋይዳ ዜጎች ወጥ ማንነት እንዲኖራቸው በማስቻል የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።

ከዜጎች የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ሙስናን በመከላከል የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑንም ገልፀዋል።
በተለይ የማጭበርበር ወንጀሎችን በማስቀረት የፋይናንስ ዘርፍ ደህንነትን ለማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል።
የፋይዳ መታወቂያ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተያዙ ግቦችን በማሳካት አበርክቶው የጎላ መሆኑንም ነው የገለፁት።
በቀጣይም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አገልግሎት ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር እንደሚሰራ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ምክትል ሀላፊ አቶ ኦላና አበበ በበኩላቸው ፋይዳ መታወቂያ የአገሪቱን ህዝብ ትክክለኛ መረጃ ለይቶ ለማወቅ መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልፀዋል።
በተለይ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚያግዝ እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ዜጎች አገልግሎት የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚያመቻች ስለመሆኑ መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026