የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ስኬታማ የፈጠራ ውጤት ባለቤቶችን ለመደገፍና ለማብቃት ትኩረት ተሰጥቷል

Apr 27, 2025

IDOPRESS

ዱራሜ፤ሚያዝያ 18/2017(ኢዜአ) :-ስኬታማ የፈጠራ ውጤቶች ባለቤቶችን ለመደገፍና ለማብቃት ትኩረት መስጠቱን የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስትቲዩት አስታወቀ፡፡


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዱራሜ ከተማ "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበለፀጉ እጆች" በሚል መሪ ሀሳብ ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጥናትና ምርምር ውድድር ሲምፖዝየምና ኤግዚቢሽን ተጠናቋል፡፡


በማጠናቀቂያው ላይ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናት፣ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ሙልጌታ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ ውጤታማ የፈጠራ ባለቤቶችን የመደገፍና የማብቃት ስራ ትኩረት አግኝቷል፡፡


በተቋማቱና በፈጠራ ባለቤቶች የሚሰሩ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለውድድር የማቅረብና ተሞክሮና ልምድ እንዲወሰዱ እንዲሁም የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸውም ይደረጋል ብለዋል።


በቴክኒክና ሙያ የሚሰጠው የስልጠናና የውድድር ስርዓቱ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ደረጃን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ይደረጋልም ብለዋል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኒክና ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ደቼ በበኩላቸው፥በክልሉ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት በዜጎች ህይወት ላይ ለውጥ የሚያመጡና ችግር ፈቺ ቴክሎጂዎች ማፍለቅ ላይ እንዲያተኩሩ መደረጉን ተናግረዋል።


በተቋማቱ እየተሰሩ የሚገኙ የክህሎትና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች የግብርናውን ዘርፍ ጨምሮ ሌሎች መርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች የምርምር ስራዎችን እያወጡ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡


እነዚህን ቴክኖሎጂዎች ወደ ማህበረሰቡ በማውረድ በኩል የሚታየውን ውስንነት ለመቅረፍ በቀጣይ በስፋት እንደሚሰራም ገልጸዋል፡፡


ከወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክህሎት ተወዳዳሪና የዋንጫ ተሸላሚ የሆነው ሰምረዲን ተማም፥ በክህሎት ዘርፍ በሰራው የፈጠራ ስራ ተሸላሚ መሆን መቻሉን ገልጿል።


መንግሥት በዚህን ወቅት የፈጠራ ስራን ለማበረታታትና ለማገዝ እያደረገ ያለው ጥረት እና የውድድሩ መዘጋጀት የክህሎትና የቴክኖሎጂን ዘርፍ ውጤታማነት በማረጋገጥና ተተኪዎች ለማፍራት ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም ተናግሯል።


በውድድሩም የወራቤ ክላስተር፣የወልቂጤና የቡታጅራ ክላስተሮች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የፌዴራልና የክልል እንዲሁም የዞንና የልዩ ወረዳዎች ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026