የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኮሌጆች ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን በማውጣት ተወዳዳሪነትን ማሳደግ አለባቸው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ሚያዝያ 18/2017(ኢዜአ):-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ችግር ፈቺ እና የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በማውጣት ተወዳዳሪነትን ማሳደግ እንዳለባቸው የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ።


ቢሮው ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ እና ከአሶሳ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር "ክልላዊ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ እና ጥናትና ምርምር ውድድር" በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም ሸንገል በወቅቱ እንደገለፁት፥ ኮሌጆች ችግር ፈቺ እና የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በማውጣት ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ይጠበቅባቸዋል።


በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለማፍራት የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተወዳዳሪዎች ባገኙት ዕድል መጠቀም እንዳለባቸው ገልጸዋል።


ውድድሩ የቴክኖሎጂ ትውውቅን በማጎልበት ችግር ፈቺ የፈጠራ ውጤቶች እንዲወጡ ያግዛል ያሉት አቶ አብዱሰላም ተወዳዳሪዎች ያካበቱትን ዕውቀት የሚያዳብሩበት ነው ብለዋል።


የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች የሚሰጡት ተግባር ተኮር ስልጠና ውጤት የሚታይበት እንዲሁም ክፍተቶችን ለመለየት የሚያስችል ውድድር መሆኑን አንስተዋል።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ የክህሎት እና ተቋማት ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ አህመድ ሙሳ በበኩላቸው የዚህ ውድድር አሸናፊዎች በቀጥታ በሀገር አቀፍ ውድድር ይሳተፋሉ ብለዋል።


የቴክኒክ እና ሙያ ዘርፍ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ እና የቴክኖሎጂ ትስስር ለመፍጠር አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።


ውድድሩ "ብሩህ አዕምሮዎች፤ በቴክኒክ የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል።


በአውቶ መካኒክ፣ ኤሌክትሪክ ስራ፣ ኮንስትራክሽን፣ በእንጨት ስራ እና በአጠቃላይ በስምንት ሙያዎች ውድድሩ ይደረጋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026