
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦ የዕዳ ሽግሽግ ድርድሮችን ጨምሮ ሌሎች ተጓዳኝ የአሰራር ማዕቀፎችን በአፋጣኝ በማጠናቀቅ ቀልጣፋ ሂደትን መከተል እንደሚገባ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ገለጹ።
በዋሽንግተን ዲሲ አየተካሄደ ካለው የዓለም ባንክ ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በዓለም አቀፉ የሀገራት የዕዳ ውይይት ላይ ተሳትፋለች።
ስብሰባው በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እና የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ እንዲሁም በወቅቱ የቡድን 20 ሊቀመንበር በሆነችው ደቡብ አፍሪካ በጋራ የተመራ ነው።
ስብሰባው በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት የሚገኝበትን ደረጃ በመገምገም የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ መወሰድ የሚገባቸውን እርምጃዎች አመላክቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደተናገሩት የዕዳ ማዕቀፉ ረጅም ጊዜ ቢወስድም ያለው ፋይዳ ወሳኝ ነው።
ይህም በዛምቢያ፣ ጋና እና አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ የተደረጉት የተሳኩ የዕዳ ሽግሽግ ጥረቶች ማሳያ እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለው በተበዳሪው ሀገር እና በአበዳሪዎች ኮሚቴ መካከል ባለው የመርህ ስምምነት መሰረት የብድር አያያዝ ውሎችና ሁኔታዎችን ይፋ በማድረግ ግልፅ አሰራርን የበለጠ ማጎልበት እንደሚገባ አመልክተዋል።
በተጨማሪም ከመርህ ስምምነት ጀምሮ ከአበዳሪ ሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነትና የመግባቢያ ሰነዶችን በመፈራረም ፈጣንና ቀልጣፋ ሂደት በማመቻቸት አላስፈላጊ መዘግየቶችን መቀነስ ተገቢ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል።
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በማርች 2025 ከአበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ መስማማቷ የሚታወስ ሲሆን እ.አ.አ. በጁን 2025 የመግባቢያ ሰነዱ ዝግጅት እንደሚጠናቀቅ የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026