የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ሂደትን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ ናት - ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ሂደትን እስከ እ.አ.አ ማርች 2026 ባለው ጊዜ ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ እንደሆነች የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ገለጹ።

በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ካለው የዓለም ባንክ ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ሂደትን የተመለከተ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ተካሄዷል።

ኢትዮጵያ በቀጣዩ ዓመት የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ዝግጅት እያደረገች ነው

ውይይቱ የተዘጋጀው በዓለም ባንክ ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የጋራ ትብብር ነው።


በመድረኩ ላይ የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዊላ፣ የዓለም ባንክ የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ምክትል ፕሬዝዳንት ንድያሜ ዲዮፕ እና የአይኤምኤፍ የስትራቴጂ ምክትል ዳይሬክተር ኬን ካንግ ተሳትፈዋል።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) የኢትዮጵያን የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬት እና ማዕቀፉ ለኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ጥያቄ ያለውን አንድምታ አንስተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያ እ.አ.አ ማርች 2026 በካሜሮን ያውንዴ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ አባል የመሆኗን ሂደት ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ገልጸዋል።


የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዊላ የኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ሂደት እንዲፋጠን የባለብዝሃ ወገን ተቋማት እና የሁለትዮሽ አጋሮች አስፈላጊውን የቴክኒክ እና የአቅም ግንባታ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ኢትዮጵያ ህግን መሰረት ባደረገው የዓለም የንግድ ስርዓት አካል ለመሆን ያሳየችውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ለኢትዮጵያ የአባልነት ሂደት ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026