
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ሂደትን እስከ እ.አ.አ ማርች 2026 ባለው ጊዜ ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ እንደሆነች የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ገለጹ።
በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ካለው የዓለም ባንክ ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ሂደትን የተመለከተ የከፍተኛ ደረጃ ውይይት ተካሄዷል።
ኢትዮጵያ በቀጣዩ ዓመት የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ዝግጅት እያደረገች ነው
ውይይቱ የተዘጋጀው በዓለም ባንክ ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የጋራ ትብብር ነው።

በመድረኩ ላይ የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዊላ፣ የዓለም ባንክ የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ምክትል ፕሬዝዳንት ንድያሜ ዲዮፕ እና የአይኤምኤፍ የስትራቴጂ ምክትል ዳይሬክተር ኬን ካንግ ተሳትፈዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) የኢትዮጵያን የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬት እና ማዕቀፉ ለኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ጥያቄ ያለውን አንድምታ አንስተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያ እ.አ.አ ማርች 2026 በካሜሮን ያውንዴ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም የንግድ ድርጅት የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ አባል የመሆኗን ሂደት ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ገልጸዋል።

የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ-ኢዊላ የኢትዮጵያ እና ኡዝቤኪስታን የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ሂደት እንዲፋጠን የባለብዝሃ ወገን ተቋማት እና የሁለትዮሽ አጋሮች አስፈላጊውን የቴክኒክ እና የአቅም ግንባታ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች ኢትዮጵያ ህግን መሰረት ባደረገው የዓለም የንግድ ስርዓት አካል ለመሆን ያሳየችውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ለኢትዮጵያ የአባልነት ሂደት ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026