የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ሀገር በቀል እውቀቶችን በማበልጸግ ለሁለንተናዊ ጥቅም በማዋል በኩል ዩኒቨርሲቲዎች የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል - ባለስልጣኑ

May 12, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ግንቦት 1/2017(ኢዜአ)፦ ዩኒቨርሲቲዎች ሀገር በቀል እውቀቶችን በማልማትና በማበልጸግ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት ጥቅም እንዲውሉ መስራት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሪክተር ወልዱ ይመስል ተናገሩ።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ ሀገር በቀል እውቀቶችን ለማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ጠቀሜታ ለማዋል የማልማትና የማበልጸግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወልዱ ይመስል፤ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል እውቀቶች ቢኖሩም እስካሁን እምብዛም ጥቅም ላይ ሳይውሉ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች ሀገር በቀል እውቀቶችን በማልማትና በማበልጸግ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት ጥቅም እንዲውሉ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያን እምቅ ሀገር በቀል እውቀቶች ለሀገር ልማትና እድገት እንዲሁም ለዓለም ዓቀፍ ተወዳዳሪነት መጠቀም ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።


የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ይስሃቅ የሱፍ(ዶ/ር)፤ በዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀቶችን ከመመዝገብና ከማደራጀት ባለፈ ለዜጎች የስራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀቶችን ለማህበራዊና የምጣኔ ሃብት ጠቀሜታ ለማዋል የማልማትና የማበልጸግ ስራን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

በእውቀት የታነፀ ትውልድ ከማፍራት ባለፈ የግብርና አሰራር፣ ግጭት አፈታት፣ ባህላዊ እውቀቶችና ሌሎች ለሀገር ጠቀሜታ ያላቸው ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።


በዩኒቨርሲቲው የሀገር በቀል እውቀት አስተባባሪ ያስሚን መሀመድ፤ ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀቶችን የመሰነድ፣ የማዳበርና ክህሎትን የማሳደግ ስራ በትኩረት እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026