የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከምግብ ፎጆታ ባለፈ ለብዙዎች የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረ ነው

Jun 5, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከምግብ ፎጆታ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረላቸው መሆኑን በጎንደር ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሴቶች ተናገሩ፡፡


በጎንደር ቀጠና የሚገኙ ሴት አመራሮች በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሞዴል በሆኑ ሴቶች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን በተመለከተ የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።


በዘርፉ ከተሰማሩ ሞዴል አልሚዎች መካከል ወይዘሮ ጽላተማርያም ተመስገን፤ በ50ሺህ ብር ካፒታል የጀመሩት የዶሮ እርባታ አሁን ላይ ወደ ሚሊዮን መሸጋገሩን ተናግረዋል።

በአራት የዶሮ ፋርሞች ከ65ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳሏቸው ጠቅሰው በልማቱ ከራሳቸው አልፈው ለብዙዎች የስራ እድል መፍጠራቸውንና ጥሩ የኢኮኖሚ አቅም እንዲገነቡ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።


ወጣት ከበቡሽ ምስጋናው በዶሮ አርባታ እንዲሁም ወይዘሮ እስከዳር ብርሃኑ በወተት ላሞች እርባታ ስኬታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር ከምግብ ፎጆታ ባለፈ ለብዙዎች የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረ መሆኑን አልሚዎቹ ገልጸዋል።


የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ደብሬ የኋላ፤ በከተማው ከ50 በላይ ኢንተርፕራይዞች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተሰማርተው እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።


የከተማ አስተዳደሩ በዚህ ዓመት በ60 ሚሊዮን ብር ወጪ ለዶሮ እርባታ ስራ የሚውሉ የክላስተር ሼዶችን በመገንባት ለስምንት ኢንተርፕራይዞች ማስተላለፉን ጠቅሰዋል።


የአማራ ክልል ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ፤ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በተለይም የሴቶችን የምጣኔ ሃብት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በርካታ ሴት ባለሀብቶችን ለማፍራት ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ጠቁመው የልምድ ልውውጡ አላማም የሴቶች ተሳትፎና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026