
ጅማ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ በተለያዩ ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ገለጸ።
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር) እንዳሉት ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርት እንዲኖር እየተሰራ ነው።
ለዚህም የሚያግዙ ዘመናዊ ጀልባዎችን በማስመጣት በሀገር ውስጥ ሐይቆች ላይ ትራንስፖርትን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ 'ጣና ነሽ 2' ለዚሁ አገልግሎት ወደ መዳረሻዋ ባህር ዳር እየተጓጓዘች መሆኑን ተናግረዋል።
ጀልባዋ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላትና ይህም ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በቀጣይም እንደ 'ጣና ነሽ 2' አይነት ዘመናዊ ጀልባዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርትን በማሻሻል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ የሚያገኘውን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ላንጋኖ እና ሻላን ጨምሮ በሁሉም ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
አያይዘውም የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ በዓለም ላይ የመዳረሻ ወደቦችን ብዛት ወደ 350 ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጭነት አቅምም ከፍ እንዲል ይደረጋል ብለዋል።
ከገቢ አንጻርም በዘጠኝ ወር አፈጻጸም የተሻለ ገቢ መገኘቱን ገልጸው፣ ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ተቋሙን ከማንዋል አሰራር በማላቀቅ የዲጂታላይዜሽን አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው ይህም ወጪን ከመቆጠብና ገቢን ከመጨመር ባለፈ ግልጽ አሰራር ለመዘርጋት ያስቻለ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅማ ከተማ ለአቅመ ደካሞች ያደሰውን መኖሪያ ቤት ለነዋሪዎች ማስረከቡ ይታወቃል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026