
ጅማ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ በተለያዩ ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ገለጸ።
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር) እንዳሉት ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርት እንዲኖር እየተሰራ ነው።
ለዚህም የሚያግዙ ዘመናዊ ጀልባዎችን በማስመጣት በሀገር ውስጥ ሐይቆች ላይ ትራንስፖርትን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ 'ጣና ነሽ 2' ለዚሁ አገልግሎት ወደ መዳረሻዋ ባህር ዳር እየተጓጓዘች መሆኑን ተናግረዋል።
ጀልባዋ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላትና ይህም ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በቀጣይም እንደ 'ጣና ነሽ 2' አይነት ዘመናዊ ጀልባዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርትን በማሻሻል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ የሚያገኘውን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ላንጋኖ እና ሻላን ጨምሮ በሁሉም ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
አያይዘውም የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ በዓለም ላይ የመዳረሻ ወደቦችን ብዛት ወደ 350 ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጭነት አቅምም ከፍ እንዲል ይደረጋል ብለዋል።
ከገቢ አንጻርም በዘጠኝ ወር አፈጻጸም የተሻለ ገቢ መገኘቱን ገልጸው፣ ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ተቋሙን ከማንዋል አሰራር በማላቀቅ የዲጂታላይዜሽን አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው ይህም ወጪን ከመቆጠብና ገቢን ከመጨመር ባለፈ ግልጽ አሰራር ለመዘርጋት ያስቻለ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅማ ከተማ ለአቅመ ደካሞች ያደሰውን መኖሪያ ቤት ለነዋሪዎች ማስረከቡ ይታወቃል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026