የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኮሪደር ልማቱ ሌሎች ከተሞች ላይ ስንመለከተው በከተማችን እንዲከናወን ስንመኘው የነበረ ነው-የቦዲቲ ከተማ ነዋሪዎች

Jun 9, 2025

IDOPRESS

ቦዲቲ፤ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ እየተከናወነ ያለው የተቀናጀ የኮሪደር ልማት በሌሎች ከተሞች ላይ ተከናውኖ ያየነውን ውጤት በከተማችንም ተፈፃሚ ሆኖ ለማየት ስንመኘው የነበረ የልማት ስራ ነው ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።


የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ12 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ስራን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።


በከተማው ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሾመ አካኮ፥ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከማሳመር ባለፈ የስራ ዕድልን ፈጥሯል ብለዋል።


በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅና ልማቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፋቸውን እንዲሚያጠናክሩም ተናግረዋል።


ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ፈቃዱ ጌታ በበኩላቸው፥ በሌሎች አካባቢ አይተውት ሲመኙት የነበረው የኮሪደር ልማት በከተማቸው በመጀመሩ መደሰታቸው ገልጸዋል።


የልማት ስራው በእድገት ላይ የሚትገኘውን የቦዲቲ ከተማን ተጨማሪ ውበትን እያጎናጸፋት እንደሚገኝ ገልፀው፥ ስራው ቀጣይነት እንዲኖረው በሚችሉት ነገር ሁሉ ለመደገፍ መዘጋጀታቸውንም ነው አስተያየት ሰጪው የገለጹት።


የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መዝገቡ ሞሬቦ፥ በከተማው የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ገልጸው፥ ለስራው ስኬታማነት የከተማው ነዋሪዎች ላሳዩት ትብብር አመስግነዋል።


ከተማውን አቋርጦ በሚያልፈው አስፖልት መንገድ ግራ እና ቀኝ ከ12 ኪ. ሜ በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ስራውን የከተማ አስተዳደሩ ከነዋሪውና ከባለሀብቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አመልክተው፥ ለስራው ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መመደቡንም ጠቁመዋል።


በከተማው የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ከግብ ለማድረስ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የመሬት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮናታን ሳሙኤል ናቸው።


በከተማው በተለዩ ዘጠኝ ስፍራዎች የኮሪደር ልማት ስራ እንደሚከናወን ገልጸው፥ ስፍራዎቹን ምቹ የማድረጉ ተግባር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።


በከተማው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማውን ውብና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድልን ያመቻቸ መሆኑም ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026