
ቦዲቲ፤ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ እየተከናወነ ያለው የተቀናጀ የኮሪደር ልማት በሌሎች ከተሞች ላይ ተከናውኖ ያየነውን ውጤት በከተማችንም ተፈፃሚ ሆኖ ለማየት ስንመኘው የነበረ የልማት ስራ ነው ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።
የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ12 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ስራን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በከተማው ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሾመ አካኮ፥ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከማሳመር ባለፈ የስራ ዕድልን ፈጥሯል ብለዋል።
በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅና ልማቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፋቸውን እንዲሚያጠናክሩም ተናግረዋል።
ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ፈቃዱ ጌታ በበኩላቸው፥ በሌሎች አካባቢ አይተውት ሲመኙት የነበረው የኮሪደር ልማት በከተማቸው በመጀመሩ መደሰታቸው ገልጸዋል።
የልማት ስራው በእድገት ላይ የሚትገኘውን የቦዲቲ ከተማን ተጨማሪ ውበትን እያጎናጸፋት እንደሚገኝ ገልፀው፥ ስራው ቀጣይነት እንዲኖረው በሚችሉት ነገር ሁሉ ለመደገፍ መዘጋጀታቸውንም ነው አስተያየት ሰጪው የገለጹት።
የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መዝገቡ ሞሬቦ፥ በከተማው የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ገልጸው፥ ለስራው ስኬታማነት የከተማው ነዋሪዎች ላሳዩት ትብብር አመስግነዋል።
ከተማውን አቋርጦ በሚያልፈው አስፖልት መንገድ ግራ እና ቀኝ ከ12 ኪ. ሜ በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ስራውን የከተማ አስተዳደሩ ከነዋሪውና ከባለሀብቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አመልክተው፥ ለስራው ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መመደቡንም ጠቁመዋል።
በከተማው የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ከግብ ለማድረስ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የመሬት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮናታን ሳሙኤል ናቸው።
በከተማው በተለዩ ዘጠኝ ስፍራዎች የኮሪደር ልማት ስራ እንደሚከናወን ገልጸው፥ ስፍራዎቹን ምቹ የማድረጉ ተግባር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
በከተማው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማውን ውብና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድልን ያመቻቸ መሆኑም ተመላክቷል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026