የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኮሪደር ልማቱ ሌሎች ከተሞች ላይ ስንመለከተው በከተማችን እንዲከናወን ስንመኘው የነበረ ነው-የቦዲቲ ከተማ ነዋሪዎች

Jun 9, 2025

IDOPRESS

ቦዲቲ፤ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ እየተከናወነ ያለው የተቀናጀ የኮሪደር ልማት በሌሎች ከተሞች ላይ ተከናውኖ ያየነውን ውጤት በከተማችንም ተፈፃሚ ሆኖ ለማየት ስንመኘው የነበረ የልማት ስራ ነው ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።


የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ ከ12 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ስራን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።


በከተማው ኢዜአ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች መካከል አቶ ተሾመ አካኮ፥ የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከማሳመር ባለፈ የስራ ዕድልን ፈጥሯል ብለዋል።


በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅና ልማቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፋቸውን እንዲሚያጠናክሩም ተናግረዋል።


ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ ፈቃዱ ጌታ በበኩላቸው፥ በሌሎች አካባቢ አይተውት ሲመኙት የነበረው የኮሪደር ልማት በከተማቸው በመጀመሩ መደሰታቸው ገልጸዋል።


የልማት ስራው በእድገት ላይ የሚትገኘውን የቦዲቲ ከተማን ተጨማሪ ውበትን እያጎናጸፋት እንደሚገኝ ገልፀው፥ ስራው ቀጣይነት እንዲኖረው በሚችሉት ነገር ሁሉ ለመደገፍ መዘጋጀታቸውንም ነው አስተያየት ሰጪው የገለጹት።


የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መዝገቡ ሞሬቦ፥ በከተማው የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ገልጸው፥ ለስራው ስኬታማነት የከተማው ነዋሪዎች ላሳዩት ትብብር አመስግነዋል።


ከተማውን አቋርጦ በሚያልፈው አስፖልት መንገድ ግራ እና ቀኝ ከ12 ኪ. ሜ በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ስራውን የከተማ አስተዳደሩ ከነዋሪውና ከባለሀብቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አመልክተው፥ ለስራው ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መመደቡንም ጠቁመዋል።


በከተማው የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ከግብ ለማድረስ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቦዲቲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የመሬት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮናታን ሳሙኤል ናቸው።


በከተማው በተለዩ ዘጠኝ ስፍራዎች የኮሪደር ልማት ስራ እንደሚከናወን ገልጸው፥ ስፍራዎቹን ምቹ የማድረጉ ተግባር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።


በከተማው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ከተማውን ውብና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካቶች የስራ ዕድልን ያመቻቸ መሆኑም ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026