የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለስራ እድል ፈጠራ ትኩረት ተስጥቷል

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ ሰኔ፣30/2017(ኢዜአ) ፡- በኦሮሚያ ክልል የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት ለስራ እድል ፈጠራ ትኩረት መስጠቱን የክልሉ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ገለጸ።

የኦሮሚያ ክልል የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ ዛሬ በጅማ ከተማ የኢንተርፕራይዞች ሽግግር እና እውቅና መርሃ ግብር አካሂዷል።


በክልሉ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ የስራ እድል ፈጠራ ዳይሬክተር አቶ ተማም ሁሴን እንዳሉት በክልሉ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

ወጣቶቹ የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደራጅተው ወደ ስራ የሚገቡበትን፣ የማምረቻ፣ የመሸጫ፣ የገበያ ትስስርና የብድር አገልግሎት በማመቻቸት ኢኮኖሚያዊ ሽግግር እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬም የጅማ ከተማ፣ ጅማ ዞን፣ አጋሮ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር እና መቱ ከተሞች የሚገኙ 120 የሚሆኑ ማህበራት ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።


የጅማ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር አስራት እሸቱ በበኩላቸው በከተማዋ በርካታ የስራ እድሎች እየተፈጠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በከተማዋ ልማትን በማፋጠን የህብረተሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በተለይ የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ቅድሚያ መሰጠቱን ገልጸዋል።

መንግስት የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ከሚሰጣቸው አቅጣጫዎች አንዱ ወጣቱን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጎልበት መሆኑን የገለጹት ደግሞ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ናቸው።

በዞኑ ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸው ይህም የወጣቶችን የኢኮኖሚ አቅም የሚያጎለብት ስለመሆኑ ተናግረዋል።


የ'መልካሙ ሀይሌና አዱኛ የህንጻ' ግንባታ ስራ ማህበር አባል ወጣት ዮናስ ታረቀኝ እንዳለው ተደራጅተው በጀመሩት የግንባታ ስራ ተጠቃሚነታቸው በማደጉ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ጠቁመዋል።

ሌላው በማህበር ተደራጅተው እየሰሩ ከሚገኙ ወጣቶችም መካከል መለሰ እና ጓደኞቹ የመንገድ ስራ ማህበር አባል ወጣት ሮባ ለገሰ በበኩሉ ተደራጅተው አነስተኛ የመንገድ ስራዎች በመስራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ሌሎች ወጣቶችም ስራ በመፈለግ ጊዜያቸውን ከማባከን ይልቅ በመረጡት የስራ ዘርፍ በመደራጀት ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው አስረድተዋል።

የክልል፣ የከተማና የዞን አስተዳደር አካላትና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026