የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋት አለብን - የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቷ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ሀገራት በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ፥ የስራ አጥነት ችግር የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ፈተና መሆኑን አንስተዋል።

የስራ አጥነት ችግርን ለማቃለል የአፍሪካ አገራት በጋራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አንስተዋል።

ስለሆነም አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የስራ ፈጠራን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ አስታውቀዋል።

ለዚህም ጥሬ ዕቃ መላክ ብቻ ሳይሆን ብዙ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እሴት ጨማሪ የምርት ሰንሰለቶችን በመዘርጋት በዜጋ ተጠቃሚነትና በወጪ ንግድ ዕድገት ላይ ትኩረት ማድረግ የግድ ነው ብለዋል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ አካታችነት ስራዎችን በማሻሻልና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

ዜጎች ለህገወጥ ስደት እንዳይዳረጉ፣ በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡና ተከብረው እንዲኖሩ አህጉራዊ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት፣ በክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ እና በህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝም አንስተዋል።

በፎረሙ የፋይናንስ አካታችነት፣ የዲጂታልና የንግድ መሰረተ ልማቶች፣ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶች፣ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026