የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቱ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማስፋት አለብን - የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም በአህጉሪቷ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት ሀገራት በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ፥ የስራ አጥነት ችግር የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአህጉሪቱ ፈተና መሆኑን አንስተዋል።

የስራ አጥነት ችግርን ለማቃለል የአፍሪካ አገራት በጋራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አንስተዋል።

ስለሆነም አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የስራ ፈጠራን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ አስታውቀዋል።

ለዚህም ጥሬ ዕቃ መላክ ብቻ ሳይሆን ብዙ የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ እሴት ጨማሪ የምርት ሰንሰለቶችን በመዘርጋት በዜጋ ተጠቃሚነትና በወጪ ንግድ ዕድገት ላይ ትኩረት ማድረግ የግድ ነው ብለዋል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ አካታችነት ስራዎችን በማሻሻልና የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመተግበር ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

ዜጎች ለህገወጥ ስደት እንዳይዳረጉ፣ በሀገራቸው ሰርተው እንዲለወጡና ተከብረው እንዲኖሩ አህጉራዊ ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት፣ በክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ እና በህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ስኬታማ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝም አንስተዋል።

በፎረሙ የፋይናንስ አካታችነት፣ የዲጂታልና የንግድ መሰረተ ልማቶች፣ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶች፣ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026