የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አፍሪ ኤግዚም ባንክ የአፍሪካን የልማት እና ትስስር ፕሮጀክቶች መደገፉን ይቀጥላል

Jul 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ለአፍሪካን የልማት እና ትስስር ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ በተጠናከረ መልኩ መደገፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ።

47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እና 7ኛው የህብረቱ ቀጣናዊ ማህበረሰቦች የመንፈቅ ዓመት የጋራ የትብብር ስብሰባ በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ተካሂዷል።


የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተሰናባቹ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ተሰናባች ፕሬዝዳንት እና የቦርድ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር ቤኔዲክት ኦርማህ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪ ኤግዚም ባንክ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጎልበትና ባንኩ ለአፍሪካ ልማት እና ትስስር የሚያደርገውን ድጋፍ የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

ሊቀ መንበሩ ባንኩ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን መከላከልን ጨምሮ ለአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትና ለኮሚሽኑ እያደረገ ያለውን ዘላቂ ድጋፍ አድንቀዋል።


በተጨማሪም ሊቀ መንበሩ ከአዲሱ የባንኩ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ(ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026