
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 15/ 2017 (ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከህብረተሰቡ ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በፋይናንስ በኩል በራስ አቅም በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባ መሆኑም ተገልጿል።
በ2017 በጀት ዓመት ህብረተሰቡ ለግድቡ ግንባታ ያደረገውን ድጋፍ፣ ትብብርና እገዛ በተመለከተ የጽህፈት ቤቱ ምክትል ስራ አስፈጻሚ ፍቅርተ ተአምር ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህ ወቅት ከቦንድ ሽያጭና ስጦታ፣ ከ8100 A አጭር የፅሁፍ መልእክት፣ ከፒን ሽያጭና ከሌሎች መንገዶች ገቢ ማሰባሰብ ማቻሉን ተናግረዋል።
በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለግድቡ ግንባታ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ድጋፍ መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡
ይህም ከዕቅድ አንጻር የ7 በመቶ ብልጫ እንዳለው ምክትል ስራ አስፈፃሚዋ አስታውቀዋል።
ፕሮጀክቱ በፋይናንስ በኩል በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ መቶ በመቶ በራስ አቅም የተገነባ መሆኑን ገልጸው፤ መላው ኢትዮጵያዊ በሞራል፣ በገንዘብ፣ በጉልበትና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ጨምሮ በአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ የተመዘገበ ስኬት መሆኑንም አስረድተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026