የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኮሪደር ልማቱ ባህር ዳር ከተማን ካላት የተፈጥሮ መስህብ ጋር ማስተሳሰር አስችሏል - ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-የኮሪደር ልማቱ ባህር ዳር ከተማን ካላት የተፈጥሮ መስህብ ጋር ማስተሳሰር ማስቻሉን የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በበጀት አመቱ በከተማው ለየት ባለ መልኩ ሁለት መሰረታዊ ግቦችን ለማሳካት ተሰርቷል።

በዚህም የመጀመሪያው የከተማውን እና የአካባቢውን ሰላም ማረጋገጥ መሆኑን ገልጸው ፤ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።


ከከተማው ነዋሪ ህብረተሰብ ጋር በተደረጉ ውይይቶችም የከተማውን ነዋሪ የሰላም ባለቤት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፤ በዚህም የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።

ትልቁ ስኬት ተደርጎ የሚወሰደው ከዚህ ቀደም ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች በጥራት እና በፍጥነት መጠናቀቃቸው መሆኑንም ገልጸዋል።

ሌላኛው በከተማው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የተሰራው የኮሪደር ልማት መሆኑንና ይህም የከተማዋን ውበት በሚጨምር መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አመላክተዋል።


የከተማዋን ፕላን ከተፈጥሮ ጋር መስተጋብር ያልተፈጠረበት ሁኔታ እንደነበር አስታውሰዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ከተፈጥሮ ጋር ያላትን መስተጋብር በማገናኘት ተጨማሪ ውበት መፍጠሩንና ተፈጥሮን አጉልቶ ማሳየት ማስቻሉን በመግለጽ።

በኮሪደር ልማቱ ላይ የተከናወኑ መሰረተ ልማቶች በተቀናጀ መንገድ በመሬት ውስጥ መዘርጋታቸውን ጠቁመዋል።

በሁለተኛው ምእራፍ የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህም 2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የማጠናቀቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ የቱሪስት መናሀሪያነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ተናግረዋል።


በተጨማሪም የፋይል ዲጂታላይዜሽንን ጨምሮ የከተማዋን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ከፍ ያደረጉ የአሰራር ስርዓቶች ተዘርግተው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

በባህር ዳር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የብልጽግና ጉዞዎችን ትክክለኛ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸው፤ የፌደራል መንግስት ለከተማዋ ልማት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ስራዎችን እየተከታተለ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይህም የሚከናወኑ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ማስቻሉን ጠቅሰው፤ ለተገኙ ስኬቶች ህብረተሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል።

በቀጣይም በተጀመረው አግባብ ከተማዋን የማስዋብ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026