
ደብረ ብርሃን ፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አስታወቀ።
የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባዔ አቶ መንግስቱ ቤተ እንደገለጹት በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች አበረታች ውጤት ተመዝግበዋል።
ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎንም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች በተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ህብረተሰቡ ተጠቃሚ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተከናወኑ ተግባራትም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ተገንብቶ ርክክብ መደረጉን አውስተዋል ።
ሌሎች እየተካሄዱ ያሉ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃና የቢሮ ህንፃ ግንባታ ስራዎች በአዲሱ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ክትትል እንደሚደረግ አመላክተዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው እንደገለጹት አስተዳደሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር ያከናወናቸው ሰላምን የማጽናትና ልማትን የማረጋገጥ ስራዎች ስኬታማ ነበሩ።
የኮሪደር ልማት፣ የመብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና ሌሎች ኢንቨስትመንትን የማስፋፋት ስራዎችን በውጤታማነት መተግበር መቻሉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ለ22ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ጠቁመው ለስራ እድል ተጠቃሚዎችም የመስሪያና የመሸጫ ቦታ፣ የብድርና ሌሎች ድጋፎች መደረጋቸውን ጠቅሰዋል።
የከተማው ማህበረሰብም ለተከናወኑ የልማት ስራዎች ከ245 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውቀዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026