የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በደብረ ብርሀን ከተማ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የተለያዩ የልማት ስራዎችም ተከናውነዋል

Jul 25, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሃን ፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አስታወቀ።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባዔ አቶ መንግስቱ ቤተ እንደገለጹት በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች አበረታች ውጤት ተመዝግበዋል።

ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎንም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች በተከናወኑ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ህብረተሰቡ ተጠቃሚ መሆኑን ጠቅሰዋል ።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተከናወኑ ተግባራትም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ተገንብቶ ርክክብ መደረጉን አውስተዋል ።

ሌሎች እየተካሄዱ ያሉ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃና የቢሮ ህንፃ ግንባታ ስራዎች በአዲሱ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ክትትል እንደሚደረግ አመላክተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው እንደገለጹት አስተዳደሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር ያከናወናቸው ሰላምን የማጽናትና ልማትን የማረጋገጥ ስራዎች ስኬታማ ነበሩ።

የኮሪደር ልማት፣ የመብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና ሌሎች ኢንቨስትመንትን የማስፋፋት ስራዎችን በውጤታማነት መተግበር መቻሉን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ለ22ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ጠቁመው ለስራ እድል ተጠቃሚዎችም የመስሪያና የመሸጫ ቦታ፣ የብድርና ሌሎች ድጋፎች መደረጋቸውን ጠቅሰዋል።

የከተማው ማህበረሰብም ለተከናወኑ የልማት ስራዎች ከ245 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026