የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተወዳዳሪና ተጠቃሚ እንድንሆን ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል- ሰልጣኞች

Jul 30, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር ፤ ሐምሌ 18/2017 (ኢዜአ) ፡- የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ክህሎታቸውን በማጎልበት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተወዳዳሪ እና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው በአማራ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጣኞች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዜጎች በዌብ ፕሮግራሚንግ ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ ፣ዳታ ሳይንስና አርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው ለማስቻል የኢትጵያዊያን ኮደረስ ስልጠና በሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ማስጀመራቸው ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎም በርካታ ወጣቶች አቅማቸውን ለማሳደግና ዘመኑን የዋጀ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለመሆን ስልጠናውን “ በኦን ላይን” ሲከታተሉ ቆይተዋል፤ ስልጠናው አሁንም ቀጥሏል።

ስልጠናው ከቀጠለባቸው የኢትዮጵያ አካባቢዎች የአማራ ክልል ይገኝበታል።

በአማራ ክልል 187 ሺህ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ወስደው በማጠናቀቅ ለምረቃ መብቃታቸው ተመልክቷል።

ስልጠናውን ከተከታተሉ ሰልጣኞች መካከል በክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ የቴክኖሎጂ ሽግግር ባለሙያ አዲሱ ፅጌ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዓለም አቀፍ ደረጃ የቴክኖሎጂ ተወዳዳሪነት እድል ያመቻቸ ነው።

የዓለም የስራ ባህል በቴክኖሎጂ ምክንያት እየተቀየረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ይህን የሚመጥን እውቀትና ክህሎት በማዳበር ተወዳዳሪ ሆኖ ለመዝለቅ ስልጠናው ወሳኝ ነው ብለዋል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ በፍጥነት እያደገ መምጣቱን አንስተው፤ በሀገሪቱ የተጀመረው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ስራዎችን ከዘመኑ ጋር አስተሳስሮ ለማከናወን የጎላ ሚና እንዳለው አመልክተዋል።

ከዘመኑ የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ለመጓዝ በአጫጫር ስልጠናዎች ራስን ማብቃት የግድ እንደሆነም ተናግረዋል።

በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መሳተፍም የቴክኖሎጂ ክህሎትን እንዳሳደገላቸውና በዓለም ዓቀፍ የስራ ውድድር ተሳታፊ እንዲሆኑ እያገዛቸው እንደሆነም ተናግረዋል።

ሌላው የዚሁ ተቋም ሰልጣኝ ይበልጣል ዓለሙ እንደገለጸው፤ ስልጠናው መንግስት ለቴክኖሎጂ እድገት የሰጠውን ትኩረት በተግባር ያረጋገጠ ነው።


በስልጠናው የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎቱን በማሳደግ ለተቋሙ ስራን የሚያሳልጡ ሶፍት ዌር ማበልፀጉን ተናግረዋል።

ስልጠናውም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደጉ ሁሉም ሰው በተነሳሽነት እንዲወስደው አስተያየት ሰጥቷል።

የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ሃላፊና የኢትዮ ኮደርስ ኢኒሸቲቭ የቴክኒካል ኮሚቴ አባል አቶ አማረ ዓለሙ፤በክልሉ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ 760 ሺህ ዜጎችን ለማሰልጠን ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በ2017 በጀት ዓመትም 191 ሺህ 992 ዜጎችን በስልጠናው ለማሳተፍ ታቅዶ 187 ሺህ ዜጎች መሰልጠናቸውን አስታውቀዋል።

ስልጠናውን ወስደው ካጠናቀቁት መካከልም 65 ሺህ የሚሆኑት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ሌሎች የስልጠና ማዕከላት ባለሙያዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በቀጣይም ዕቅዱን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ኢኒሼቲቩ በተቀናጀ መንገድ እንደሚተገበር አንስተዋል።

አሁን ላይ በስልጠናው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ዜጎች ቁጥር በእጅጉ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026