
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 20/2017(ኢዜአ)፦የሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባዔ ተሳታፊዎች ማዕከሉን መጎብኘታቸው ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ ገለጹ።
በኢትዮጵያ፣ በጣልያን እና በተመድ ትብብር የተዘጋጀው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባኤ እስከ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከተለያዩ አገራት የመጡና የሁለተኛው የመንግስታቱ ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከልን ጎብኝተዋል።
የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢኒስቲትዩት ስር ከሚገኙ 22 የምርምር ማዕከላት አንዱ ነው።
የምርምር ማዕከሉ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እያደረገች ያለውን ጥረት ከዳር ለማድረስ ዓይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ እንደገለጹት፤ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ መነሻነት ማዕከሉ መጎብኘቱ በግብርናው ዘርፍ የሚደረገውን ትብብር ያጠናክራል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026