የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በከተማው የነዋሪውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

ጉደር፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦በጉደር ከተማ የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ገለጸ።

የጉደር ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚልኬሳ ደንደና ለኢዜአ እንደገለጹት፥በበጀት ዓመቱ በከተማዋ የህዝቡን የልማት ጥያቄ የሚመልሱ መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ ናቸው።

ለአብነትም አዲሱን ማስተር ፕላን ተከትለው እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም ፈጥረዋል ብለዋል ፡፡


ከግንባታዎቹ መካከልም የመንገድ ዳር ማስዋብ፣ የአደባባዮች፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቦዮችና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያቀፈው የኮሪደር ልማት ስራ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኮሪደርና ሌሎች በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ስራዎች ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ያሳድገዋል ብለዋል።

የከተማዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ ያለመ ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ ከአምቦ ከተማ የውሃ ቦርድ ጋር በመተባበር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በከተማዋ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽት ለማስፋትም በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባቱን አንስተዋል።

በከተማዋ ከሚከናወኑት የ4 ኪሎ ሜትር አዲስና ነባር መንገዶች ግንባታ መካከል 2 ኪሎ ሜትሩ የውስጥ ለውስጥ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ከተማዋን ከገጠር ቀበሌዎች ጋር የሚያተሳስር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጉደር ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ በቀለ ጋቢሳ በበኩላቸው፤ በከተማው አስተዳደር እና በሕብረተሰቡ ተሳትፎ እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ በመሆናቸው የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።

በተለይም የኮሪደር ልማቱ ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠርና ከተማዋን ለቱሪስት ምቹ ለማድረግ በማገዙ ተግባሩን በመደገፍ በፍጥነት ለአገልግሎት እንዲበቃ እንደሚሰሩም አመልክተዋል፡፡

ሌላኛው የከተማው ነዋሪ አቶ አለማየሁ ደንደና በበኩላቸው ከተማዋ ከኮሪደር ልማቱ በፊት አብዛኛው የንግድ ቤቶች በፕላስቲክ መሸፈናቸው የከተማዋን ውበት ከመቀነሳቸው ባለፈ በህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ላይ ችግር መፍጠራቸውን ተናግረዋል ።


የኮሪደር ልማቱ ጠባብ የነበሩ መንገዶችን በማስፋት የነዋሪውን የልማት ተጠቃሚነት ለማሳደግና ለወጣቶች አማራጭ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026