
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦ ጅግጅጋ ለሶማሌ ክልል ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ እንደምትገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች የጅግጅጋ ከተማን የኮሪደር ልማት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት የምስራቋን ኮከብ ወርቃማ የውበት ደባብ አልብሷታል ብለዋል።

በከተማዋ በምሽት ተዘዋውረው ባደረጉት ምልከታ ከስምንት ወራት በፊት በሁለት ምዕራፍ የተጀመሩ ስራዎች በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መሆናቸውን መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን የአስፋልት መንገዶች ያሰፋ፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችንም ያካተተ መሆኑን አድንቀው፥ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች ትኩረት እንደተሰጣቸውም ገልጸዋል።
የወጣቶችና ታዳጊዎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ ጣቢያዎችም በመገንባት ላይ ናቸው ብለዋል።
ከተማዋ ለክልሉ ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ መሆኗንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።
የከተማዋ የቆየ ችግር የነበረውን ጎርፍ መከላከል የሚያስችሉ ማፋሰሻዎች፤ የተቀናጀ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮምና የመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታዎች የሚያበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በከተማዋ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ባለሀብቶች በከተማዋ በሆቴል አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ተሰማርተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉም ነው ያሉት።
በጅግጅጋ ከተማ በሁለት ምዕራፍ የ30 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026