የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ለልማት እቅዶች መሳካት በትኩረት ይሰራል- ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ለልማት እቅዶች መሳካት በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር በዲጂታል የእቅድ ክትትልና ግምገማ ስርዓት እና በልማት ፕሮጀክቶች አስተዳደር ዙሪያ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ እንዳሉት፤ በክልሉ የዲጂታል አገልግሎትን በማስፋት ለልማት እቅዶች መሳካት በትኩረት ይሰራል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘመናዊና የተሳለጠ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ካለው ፋይዳ በተጨማሪ ስራዎችን ከርቀትና ከየትኛውም ቦታ ሆኖ ለመምራት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

እንዲሁም በክልላዊም ሆነ በሀገራዊ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረቱ የልማት ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና ፕሮጀክቶችን ለመቅረጽና ውጤታማነታቸውን ለመከታተልና ለመገምገም የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።

በመሆኑም የዲጂታል ቴክኖሎጂን በማስፋት የታለመውን የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።


የምክክር መድረኩም በክልሉ ያለውን የመረጃ አያያዝ ስርዓትና በዲጂታል የእቅድ ክትትልና ግምገማ ረገድ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን የሚያቃልል መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሯ አመልክተዋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመከታተልና ስኬታማ ለማድረግ ዘመኑ ያፈራቸውን የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል።


የምክክር መድረኩ ዓላማም የዲጂታል እቅድ ክትትልና ግምገማ ስርዓትን ወደ ክልል በማውረድ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ለማሳለጥ መሆኑን ተናግረዋል።

በመድረኩ ላይ በዲጂታል የእቅድ ክትትልና ግምገማ ስርዓት፣ በመንግስት የልማት ፕሮጀክቶች አስተዳደርና አመራር እንዲሁም በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026