የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የምርት ብክነትን ለመቀነስና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ሜካናይዜሽን በስፋት ጥቅም ላይ የማዋሉ ተግባር ይጠናከራል

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፡-የድህረ ምርት ብክነትን ለመቀነስና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሩ የግብርና ሜካናይዜሽንን በስፋት ጥቅም ላይ እንዲያውል የሚደረጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የምርት ብክነትን በመቀነስ የዜጎችን የምግብ ዋስትና እና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።

ከዚህ ውስጥም አርሶ አደሩ ሜካናይዜሽን የሆኑ የመውቂያ፣ የማጨጃና የምርት መሰብሰቢያ መሳሪያዎችን እንዲጠቀም በማድረግ የምርት ብክነትን ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።

በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ለኢዜአ እንዳሉት ግብርናውን በማዘመን የምርት ብክነትን ለመቀነስ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው።

በተለይም ሰብል በሚዘራበት፣ በሚወቃበትና በሚሰበሰብበት ወቅት ሜካናይዜሽን የእርሻ መሳሪያዎችን በማሰራጨትና አርሶ አደሩ ጥቅም ላይ እንዲያውላቸው እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በአሁኑ ወቀት በተለይም የበልግ ምርት የሚሰበሰብበት ወቅት በመሆኑ ብክነትን ለመቀነስ የተጠናከሩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዋናነትም ስንዴ በሚያመርቱ አካባቢዎች የመውቂያ ኮምባይነር በስፋት እየተሰራጨ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ምርታና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀም እየተደረገ ነው።

በተለይም በኩታ ገጠም የሚያርሱ አርሶ አደሮችን በማደራጀት በጋራ እንዲሰሩና የምርት ብክነትን እንዲከላከሉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የምርት ብክነት ከዘር ወቅት አንስቶ ምርቱ ወደ ጎተራ እስኪገባ የሚከሰት በመሆኑ አርሶ አደሩ ዘመናዊ እርሻ መሳሪያዎችን እንዲጠቀም እየተደረገ ነው ብለዋል።

በተለይ አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ብክነት የሚደርሰው በሚጓጓዝበት ወቅት በመሆኑ በዋናነት ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች የተሻሉ ማጓጓዛዎች እንዲጠቀሙ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ብክነትን መቀነስ ምርትና ምርታማነትን መጨመር ነው የሚሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ብክነትን ለመቀነስ የሚከናወኑ ተግባራት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ በአገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026