የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያውያን ትብብር በጉባ ሠማይ ስር ታላቁ የሕዳሴ ግድብንና የንጋት ሐይቅን ማብሰር አስችሏል -ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያዊያን ትብብር በጉባ ሠማይ ስር ታላቁ የሕዳሴ ግድብንና ትውልድ ተሻጋሪውን የንጋት ሐይቅ ማብሰር ማስቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ - የንጋት ሐይቅ የረቂቅ ማስተር ፕላን ጥናት ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፥ ለትውልድና ታሪክ የሚሻገር አሻራን ለማስቀመጥ አብሮና ተባብሮ መስራት መታደል ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያውያን በተባበረ አቅማቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በጉባ ሰማይ ስር በመገንባት ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ትልቅ የልማት ሥራ ማሳካታቸውን ገልጸዋል።

የሕዳሴ ግድብ ስኬትም ዜጎች የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ እና የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ቁልፍ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የግድቡ ሰው ሰራሽ የሆነው ንጋት ሐይቅ የሚሸፍነው 240 ኪሎ ሜትር ርዝመትና ከ74 ቢሊዮን ሜትር ኪዩቢክ በላይ የውሃ መጠን ለኢትዮጵያዊያን ዘርፈ ብዙ ትሩፋት እንዳለው አስገንዝበዋል።


የንጋት ሐይቅን በተደራጀና ራሱን በቻለ ማስተር ፕላን ለመምራት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በማንሳት፥ ይህም ሐይቁ ተጠብቆ ከትውልድ ትውልድ እንዲሸጋገርና ዜጎች ከትሩፋቱ ተቋዳሽ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።

የሕዳሴ ግድብ - የንጋት ሐይቅ የረቂቅ ማስተር ፕላን በዓሳ ምርታማነት፣ በውሃ ዘላቂነት፣ በቱሪዝምና በአስተዳደር ውጤታማ ሥርዓት ለመዘርጋት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፍላጎት ፍትሐዊ የጋራ ልማት ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ መሆኑን ጠቁመው፥ የሕዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አስረድተዋል።

በንጋት ሐይቅ የረቂቅ ማስተር ፕላን ጥናት ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ ላይ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026