የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፍ ለማድረግ የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው- ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ 

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፍ ለማድረግ የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

''የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት'' በሚል መሪ ሃሳብ 6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ዘመኑን በሚመጥን መንገድ በቴክኖሎጂ የታገዘና ደህንነቱ የተጠበቀ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በክልሉ የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፍ ለማድረግ የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ቴክኖሎጂን በማልማትና በመተግበር የተጀመሩ ስራዎች በትብብርና በቅንጀት የሚተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

የኢንፎርሜሸን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ ላይ መሆኗን ጠቅሰው ፤ በዚሁ ልክ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አስረድተዋል።


የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የመፍታት፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን አንስተው፤ ከዚሁ ጋር በተገናኘ የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የግድ መሆኑን ገልጸዋል።

የሳይበር ደህንነት ወር የመከበሩ ዓላማም ተቋማትና አጠቃላይ ሕብረተሰቡ በሳይበር ደህንነት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማስቻል መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር ብሎም በዲጂታላይዜሽን የስማርት ከተሞች እድገት ጉዞ ላይ የተቋማትን የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት በመቀነስ ዲጂታል ኢትዮጵያን ትልም ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ከጥቅምት 1 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ መርሀ ግብሮች መከበሩ የሚቀጥል መሆኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026