🔇Unmute
ባሕርዳር ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፍ ለማድረግ የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
''የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት'' በሚል መሪ ሃሳብ 6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ዘመኑን በሚመጥን መንገድ በቴክኖሎጂ የታገዘና ደህንነቱ የተጠበቀ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም በክልሉ የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፈጣንና ቀልጣፍ ለማድረግ የሚያስችል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ ቴክኖሎጂን በማልማትና በመተግበር የተጀመሩ ስራዎች በትብብርና በቅንጀት የሚተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
የኢንፎርሜሸን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ ላይ መሆኗን ጠቅሰው ፤ በዚሁ ልክ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አስረድተዋል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የመፍታት፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ጊዜው የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን አንስተው፤ ከዚሁ ጋር በተገናኘ የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የግድ መሆኑን ገልጸዋል።
የሳይበር ደህንነት ወር የመከበሩ ዓላማም ተቋማትና አጠቃላይ ሕብረተሰቡ በሳይበር ደህንነት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማስቻል መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር ብሎም በዲጂታላይዜሽን የስማርት ከተሞች እድገት ጉዞ ላይ የተቋማትን የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት በመቀነስ ዲጂታል ኢትዮጵያን ትልም ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
6ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ከጥቅምት 1 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ መርሀ ግብሮች መከበሩ የሚቀጥል መሆኑ ታውቋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026