የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ እንደገና እንድትሰራ አድርገዋል - አቶ አገኘሁ ተሻገር

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ ለአፍሪካ ከተሞች ምሳሌ እንድትሆንና እንደገና እንድትሰራ በማድረግ የላቀ ሚና መወጣታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሐ ግብር አካሂዷል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ መንግሥት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በጥራት እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።


ለዚህም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት በቂ ገቢ ለመሰብሰብና ሀገራዊ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የፌደራል መንግሥትም ሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢ የመሰብሰብ አቅማቸው እያደገ ነው ያሉት አቶ አገኘሁ፥ በዚህም የማህበረሰቡን ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት እያረጋገጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ለዚህ ደግሞ የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፥ በከተሞች እድገት፣ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ሌሎች ዘርፎች ጉልህ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

የአዲስ አበባን አዳጊ ፍላጎት በበቂ ደረጃ ለማሟላት የገቢ ሰብሳቢ ተቋማትና ግብር ከፋዮች ይበልጥ ተቀናጅቶ መስራትና ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በገቢ ዘርፍ ሪፎርሙ የታክስ አሰባሰብና አስተዳደር ስርዓትን በማሻሻል የሚሰበሰበው ገቢ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፥ ታማኝ ግብር ከፋዮች ለሀገርና ለከተማዋ ልማት ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነዋል።

በአዲስ አበባ የሚታየው ሁለንተናዊ ለውጥ ያለታማኝ ግብር ከፋዮች ይሳካል ተብሎ እንደማይታሰብ በመጠቆም፥ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ ከተማ እንደገና እንድትሰራ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ለከተማዋ ዕድገት በተለይም አዲስ አበባን የአፍሪካ ከተሞች ምሳሌ እንድትሆን እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል።

የመዲናዋ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አበክሮ መስራት እንደሚገባ በግልፅ፥ የግብር ከፋዩን መሰረታዊ አገልግሎትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየጊዜው እየፈተሹ መፍትሄ መስጠትን የትኩረት ማዕከል ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026