የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጉራጌ ዞን የተሻሻሉ የዳልጋ ከብት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ ተችሏል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ ፤ ጥቅምት 11/ 2018 (ኢዜአ)፡- በጉራጌ ዞን የተሻሻሉ የዳልጋ ከብት ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ መቻሉን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ።

በዞኑ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ማስጀመሪያ መረሃ ግብር በእንደጋኝ ወረዳ ገነት ቀበሌ ዛሬ ተካሂዷል።

በዚህ ወቅት የመምሪያው ምክትል እና እንስሳት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሙደሲር፤ በዞኑ የዳልጋ ከብት ዝርያንና ጤና አጠባበቅ በማሻሻል ምርታማነታቸውን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

የእንስሳቱ ዝርያ መሻሻልም የወተትና የስጋ ምርትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያደገ መሆኑን ገልጸዋል።

ለአብነት ከነባሩ ዝርያ በቀን በአማካይ ይገኝ የነበረን ሁለት ሊትር ወተት ዝርያቸው ከተሻሻሉ ላሞች ምርቱን በእጥፍ ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል ።

ስራውን ለማስፋትም በተያዘው በጀት ዓመት ከ32 ሺህ 490 በላይ እንስሳትን ለማዳቀል ግብ ተይዞ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።

የእስሳት ዝርያውን ከማሻሻል ባለፈም ለመኖ ልማት ትኩረት በመሰጠቱ 8 ሺህ 946 ሄክታር ማሳ የእንስሳት መኖ በኩታ ገጠም እየለማ እንደሆነም አክለዋል።


የእንደጋኝ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉቀን ገዙ ፤ በእንስሳት ዘርፍ ያለው ፀጋ በመጠቀም የአርሶአደሩን ኑሮ ለማሻሻል በተከናወነው ስራ የተገኘውን ውጤት ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

አርሶ አደሩ ከእንስሳት ቁጥር በመውጣት ኢኮኖሚ ጠቀሜታቸው ከፍ ያሉ የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው የዳልጋ ከብቶች እርባታ ላይ እንዲያተኩር መሰራቱን አንስተዋል።

በሰው ሰራሽ ዘዴ ከተዳቀሉ ላሞቻቸው የተሻለ የወተት ምርት በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የእንደጋኝ ወረዳ አርሶ አደር ሽኩሪያ የኑስ ናቸው።

ዝርያቸው ከተሻሻለ ላሞች በሚያገኙት የወተት ምርት ሽያጭ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ከማደጉ ባለፈ ከጥጆች ሽያጭ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌላው የወረዳው አርሶ አደር በህሩ አብደላ፤ የተሻሻሉ ላሞች በማርባት ቀደምሲል ከሚያገኙት ምርት ከፍ ብሎ በቀን ከ10 ሊትር በላይ ወተት እያገኙ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026