የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የዲጂታል መታወቂያ በተለያዩ አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችል የአገልግሎት ማዕከላትን የማስፋት ስራ እየተከናወነ ነው

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018 (ኢዜአ):-የዲጂታል መታወቂያ አገልግሎትን በተለያዩ አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችል የአገልግሎት ማዕከላት ማስፋት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ገለጹ፡፡

እስካሁን ከ27 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የምዝገባ አስተባባሪ ደጀኔ ገብሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ለሁሉም ነዋሪዎች ዲጂታል መታወቂያን በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ ሰፋፊ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

የምዝገባ አገልግሎቱን በተለያዩ የአገሪቷ አካባቢዎች ለማዳረስ ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የአገልግሎት ማዕከላት በማስፋት ምዝገባ እያካሄደ ነው።

በተጨማሪም አገልግሎቱ ወደ ሩቅ አካባቢዎች እንዲደርስ በተንቀሳቃሽ የምዝገባ ጣቢያዎች (Mobile Registration Units) አማካኝነት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ከአምስት ሺህ በላይ የመመዝገቢያ ማሽኖች አገልግሎት ላይ ናቸው ያሉት አስተባባሪው፤ ከ27 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል ብለዋል።

እስከ በጀት ዓመቱ አጋማሽ ድረስ የመመዝገቢያ ማሽኖቹን ቁጥር ወደ 10 ሺህ በማሳደግ ተደራሽነትን ለማስፋት መታቀዱን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በዓመቱ ውስጥ 60 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ይህንኑ ለማሳካት ጠንካራ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስተባባሪው አስረድተዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የዲጂታል ኢኮኖሚውን በማሳደግ፣ የገንዘብ ማጭበርበርን በመቀነስ እንዲሁም የመንግሥትና የግል አገልግሎቶችን ይበልጥ ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026