የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሕጋዊና ታሪካዊ ተቀባይነት ያለው ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ጉዳይ ነው - አምባሳደር ጥሩነህ ዜና

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 25/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን የማስመለስ ጥያቄ ሕጋዊና ታሪካዊ ተቀባይነት ያለው ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ጉዳይ መሆኑን አንጋፋው ዲፕሎማት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ገለጹ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ጥቅምት 18/2018 ዓ/ም ማካሄዱ ይታወቃል።

በዚሁ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረት ያለው ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ አካል የነበረውን የባሕር ጠረፍ ለማጣት 30 ዓመት በላይ የወሰደውን ያህል የትግል ታሪክ አሁን ላይ ወደ ባሕር በር ለመመለስ ሌላ 30 ዓመት እንደማይወስድባት አጽንኦት ሰጥተዋል።

የቀይ ባሕር ባለቤትነትን ጥያቄ ለመፍታት የተረጋጋ፣ የሰከነና በውይይት ላይ የተመሰረተ አካሄድ መከተል ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለማጣት የፈጀውን ያህል ለመመለስ አይፈጅም ብለዋል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድም ሕጋዊና ተቋማዊ መሠረት የሌለው የሚያስቆጭ የብሔራዊ ጥቅም ስብራት አካል መሆኑን አስረድተዋል።

አንጋፋው ዲፕሎማት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበት መንገድ ሕጋዊና ታሪካዊ ቅቡልነት የሌለው ጉዳይ ነው።

ኢትዮጵያ ከ1983 ዓ.ም በፊት በነበረው ታሪኳ የባሕር በር ባለቤትነቷን አስጠብቃ የቆየች ሀገር ብትሆንም በታሪካዊ ጠላቶች ሴራ ከቀይ ባሕር እንድትገለል መደረጉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚጋልቧቸውና ህጋዊ መሰረት የሌላቸው አካላት ምንም አይነት የህዝብ ምክክር ሳያደርጉ የባሕር በርን ያህል ግዙፍ የብሔራዊ ጥቅም አንኳር ጉዳይ ማሳጣታቸውን አስታውሰዋል።

በህዝብ የተመረጠ ሕጋዊ የመንግስት አስተዳደር ባልነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተገለለችበት መንገድ ጉልህ ዓለም አቀፍ የሕግ ጥሰት የተፈጸመበት የታሪክ ስብራት መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የአሁኑ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም ህዝባዊ መሠረት ያለው የጋራ ተጠቃሚነት መርህን የተከተለ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ጉዳይ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት።

በዚህም የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት የማስመለስ አካሄድ በታሪካዊ ዳራ የተደገፈ ሕጋዊ መሠረትና ተቀባይነት ያለው መሆኑን አስረድተዋል።

መንግስትም የኢትጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ለማስመለስ እየተከተለ የሚገኘው በሳል የዲፕሎማሲ አካሄድ የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከጥንተ አክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ የቀይ ባሕር ቀጣናን ሰላምና ደኅንነት በማስጠበቅ የባሕሩ ባለቤትና ተጋሪ ሀገር እንደነበረችም ነው አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ያስታወሱት።

በፖለቲካ ሴራ ከአካባቢው እንድትርቅ መደረጉ የቀይ ባህር ቀጣና የአሸባሪዎች መናኸሪያ በመሆን ለቀጣናው ሰላምና ደኅንነት መታወክ መንስኤ እየሆነ መጥቷል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ የሚያሻው ጉዳይ መሆኑና ብሔራዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ ባለፈ የቀጣናውን ደኅንነት በማስጠበቅ ለዓለም አቀፍ የሚተርፍ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው አንስተዋል።

ኢትጵያውያን፣ የቀጣናው ሀገራትና የዓለም ህዝብ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ምክንያታዊ ጥያቄ በጎ ምላሽ እንዲያገኝ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026